አዲስ አበባ፤ ሸዋ የአማራዋ መዲና ናት ስንል....
ኢህአዴግ በአሁኑ ውሳኔው የኦሮምያን ልዩ ጥቅም በአዲስ አበባ ለማስከበር አረቀቅኩት ያለው አዋጅ ፤ በእርግጥም እንደሚፀድቅ ተማምኖ ማቅረቡ ፤ ያልበሰለ እና ታሪካዊ የአማራን ድርሻ እና ባለቤትነት ያገለለ አሰተሳሰብ በመሆኑ ሊታረም ፣ ሊታይ እና ሌሎችም በሄሮች እና ብሄረሰቦች እንዲሁም ፣ የሽዋ አማራው በአዲስ አበባ ምክር ቤት ወንበር የመወሰን መብቱ ሊጠበቅለት ይገባል። አዲስ አበባ አማራው ራሱን ሰውቶ ያነገሳት ከተማ ናት። ለአማራው ልዩ ጥቅምም በአዲስ አበባ ከምክር ቤት ወንበር ጀምሮ እስከ ሰሜን ሽዋ የአማራ ክልል ዞን ልዩ ተጠቃሚነት የታሪክ ባለቤትነቱ ሊገለል አይገባም።
"የአማራ" መንግስት ስርዓት ውስጥ "የሸዋ አማሮች" አዲስ አበባን መርጠው ፣ ቆርቁረው ፣ አደራጅተው እና አሳድገው ለሀገር እና ለአለም ዲፕሎማሲያዊ መቀመጫነት አብቀተዋታል የ"ብሄረተኞነት"ከተማ ሳይሆን የሁሉም ብሄርች ከተማ መናገሻ አድርገዋትል። ይህ አፈታሪክ አይደለም ማንበብ ለሚችል ሰው Sorenson, Imagining Ethiopia , (New Brunswick, NJ Rutgers University Press) p.12 ወይም Messay, p.36 ፣ እና Ibid., p.23 እንዲሁም Taddesse,1972,pp 132 -135; Bahiru, p.75; Donald, C.pp.21 -22 ያገላበጠ አንባቢ ሁሉ አያጣውም። ብዙሃኑ "የሸዋ አማራ" ያቆማት እና ዙፋኑን ያፀናባትን ከተማ የአንድ ብሄር ተጠቃሚነትን ብቻ ባረጋገጠ ሁኔታ ከፖለቲካዊ ቁማርነት እየገፉ ፣ የአንድ በሄር እንብርት ናት። ሲሉ ማውራት ለኔ ትንሹ ልጅ ሲያለቅስ ትልቁን አንተ ዝም በል ብሎ የትልቁን ንብረት ቀምቶ እንደመስጠት ነው ምቆጥረው ።
አዋጁ ፍትሃዊ ማይሆነው እኩል ተጠቃሚነትን ሳይሆን የአንድ ቡድን ውቅታዊ ጥያቄ ለመመለስ ያለመ መሆኑ ላይ ማተኮሩ ነው። በእርግጥም የመንን ፣ ቀይ ባህርን ፣ ኤርትራን እና ጅቡቲን አንድም በአቅም እጥረት አልያም በፖለቲካ ድክመት እያሳለፍን ታሪካችንን ሽጠን በልተነዋል። ከታሪካዊ ባለቤትነት ይልቅ የፖለቲካ ጥቅም የሚያሸንፈው መንግስት በተፈጠረበት ጊዜ ሁሉ ብዙ ነገር ከእጃችን ወድቋል። ሀገርን መገንባት ሳይሆን ብሄርን በመገንባት በተጠመደ ስርዓት ውስጥ ደግሞ አንድን በር መዝጋት ብዙ ሽህ በሮችን እንደመክፈት ይቆጠራል ይታያልም። አዲስ አበባን መስርተው ፣ ጠቅመው ፣ የመንግስት አመራር መዋቅር ሹመው፣ አብዛኛውን የኢኮኖሚ ምንጮች አፍልቀው፣ የአዲስ አበባን የግዛት ክፍሎች ይገዙ የነበሩ፣ የአዲስ አበባ መስራች ና ፈጣሪዎች ለኢኮኖሚ እንቅስቃሴያቸው አዲስ አበባን ማዕከል አድርገው የመሰረቱ ነበሩ። የአማራ ህዝብ የሸዋ መኳንንቶች ምስጋና ይግባቸው እና የሁሉም ብሄሮች መኖሪያ አድርገዋታል።
በቅርቡ በተካሄደ ጥናትም የብሄር ማንነት የሌለው ሰፊ ህዝብ የሚኖርበት ክልል አዲስ አበባ ነው። ከ63 በመቶ በላይ የሚሆነው አማራ በሆነባት ከተማ መሬቱን የአንድ ብሄር ሃብት አድርጎ ማውጅ ምን አይነት ብስለት የጎደለው አሰራር መሆኑን ያሳያል።
ብዙሃኑ የሸዋ አማራ በድህነት እየኖረ ስልጣን አልባና እንደ አንድ ቡድን በየስርዓቱ እየተመዘበረ ባድማው ውስጥ ራሱን መፈለግ ወጋችን ፣ ታሪካችንም ነው። ይህ አዲስ አበባ ባለዎለታዋን የምትዘነጋ ከተማ አይደለችም ለእምየ ሚኒልክ ሃውልቷን ፊቱን ኦዞራ ያቆመችው በምሃል ጊዩርጊስ ወደ መንበሯ "የሸዋ አማራ ሀገር" ነው። ታዲያ እንዴት ነው በኦሮሞ የተከበበችው አዲስ አበባ ፊንፊኔ ብቻ ምትሆነው። ቋንቋዋን ምትቀይረው። የሌላው ብሄር ልጆችስ በአባታቸው ባድማ ወዴት ይወድቃሉ???
የማይመለሱ ብዙ ሽህ ጥያቄዎች ቢኖሩም ያባቶቻችንን ርስት አንሰጥም ብያለሁ እና አማራ አዲስ አበባን የሚያውቃት ማንም ከሚያውቃት በፊት ነው። Pankhurst Rassam አገላለጽ ጎንደር በ19ኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ አጋማሽ ከሰሜን፣ ከምእራብና ከደቡብ ለሚነሱ የሲራራ ነጋዴዎች ሁነኛ ማረፊያ ማዕከል ነነበረች በዚያ ዘመን ከጎንደር ወደ ማህል አገር የሲራራ ነጋዴዎች መተላለፊያ በርካታ አቅጣጫዎችና ቅርንጫፎች ነበሩት። በዚህም አንዷ አዲስ አበባ እንደነበረች በመፅሓፋቸው ከትበውታል።
ከጎንደር ሰፈራቸው የተነሱ ነጋዴዎች በጣና ሃይቅ በኩል አድርገው ወደ ይፋግ ከተሻገሩ በሁዋላ በሁለት በመከፈል አንዱ ወገን ወደምስራቅ አቅጣጫ ወደ ሸዋ (አዲስ አበባ) ሲያቀና ሌላኛው ወገን ደግሞ ወደደቡብ ወደ ጎጃም ያመራል። ወደ ደቡብ አቅጣጫ የሚዘልቀው የንግድ መስመር፣ ባሶ፣ ጉድሩ፣ በማቋረጥ ወደ ጎንደር መጥተው በጨውና ከውጭ አገር በሚገቡ እቃዎች የሚለወጡ "ወርቅ፣ የዝሆን ጥርስ፣ የከርከሮ ቀንድ፣ የግስላ/ ነብር ቆዳ፣ የጉማሬ ቆዳና ጋሻ እንዲሁም የባሮች" ምንጭ ወደሆኑት ከፋና ጃንጀሮ ይደርሳል ። ከእነዚህ በተጨማሪ ነጋዴዎች በሸዋ (አዲስ አበባ)፣ በሐረርና በዘይላ በኩል በማለፍ ወደ ሶማሌ የበርበራ ወደብ፣ "የዝሆን ጥርስ፣ ባሮችና ፈረሶች" ይዘው በመሄድ በልዋጩ ብረት፣ ጥጥና የህንድ ሸቀጦችን ለአገር ውስጥ ገበያ ያቀርቡ ነበር ።
አገር አቋራጭ ንግድ ወይም የሲራራ ንግድ በአማራ ክልል ለነበሩት በርካታ ገበያዎችና የንግድ ማእከላት መፈጠር ዋንኛ ሚና ተጫውቷል። በ18ኛውና በ19ኛው ምእተ አመታት የጎንደር ፣ የጎጃም እና የሽዋ ነጋዴዎች ምቹ መደላድል የፈጠሩባት እና ጠምደው ያረሱበት ርስታቸው ናት።
ለመሬት ባለቤትነት ታሪክ ተያይዞ የሚጠራው የንግድ መስመር ሲሆን በ19ነኛው ምእተአመት መጀመሪያ ላይ ከፍ ያለ ኢኮኖሚያዊ ጥቅም ከነበራቸው የንግድ መስመሮች የሸዋው የንግድ መስመር ነው። አጼ ሚኒልክ የመንግስታቸውን መቀመጫ ከተማ ከአንኮበር ወደ እንጦጦ ከማዘዋወራቸው በፊት አንኮበር፣ አንጎለላና አልዩ አምባ የታወቁ የገበያ ማእከላት በመሆን አገልግለዋል። በተለይ አንጎለላ ወደ ሰሜን፣ ምስራቅ፣ ምእራብና ደቡብ የሚጓዙ የአማራ፣ የኦሮሞ፣ የሶማሌ፣ የጉራጌ፣ የሐረሬና የደንከሌ ነጋዴዎችን ቀልብ የሚስብ የንግድ ማእከል ነበር።
ከሸዋ የንግድ መስመር ወደሰሜን አቅጣጫ በአድዋና በአንጣሎ አድርጎ የጎንደርና የሸዋ ሲራራ ነጋዴዎች መገናኛ ወደነበረው ምጽዋ የሚደርስ ነበር።
የጎጃም ነጋዴዎችም ወደ ሰሜን የሚያልፍ ሌላ የንግድ መስመርም ነበራቸው። ከዳንግላ ባሪያ፣ ከዘጌ ቡና ጭነው ወደ ጎንደር የሚነግዱ ነጋዴዎች በቡሬ፣ በዳንግላ ወይም ዘጌ በይስማላና በደልጊ አድርገው ወደ ጎንደር ይደርሳሉ። ከወሎና ከምስራቅ ጎጃም የሚነሱ ነጋዴዎች ደግሞ በደጀንና በብቸና በኩል አድርገው እንጦጦ ይሰፍራሉ። በሞጣ፣ አዴት፣ ወረታ አድርገው የሚጓዙት ወደ አገራቸው ወደ ደሪጣ የሚገቡት ነጋዴዎች ጭነታቸውን ደሪጣ ካላራገፉ በእንፍራዝና በምንዝሮ በኩል ተሻረው ጎንደር ይገባሉ። ወደ ታጁራ ወደብ የሚነግዱ የወሎና የአማራ ሳይንት ነጋዴዎች ደግሞ በብቸና፣ ቃሉ፣ ወረሂመኑና ደሴ አድርገው ይጓዛሉ። ንጉስ ተክለ ሃይማኖት በ1878 ዓም በእንባቦ ጦርነት በአጼ ምኒሊክ ድል እስከሆኑበት ድረስ ባሶ የደራ የንግድ ማእከል በመሆን አገልግሏል። የጎጃም የሽዋ እና የጎንደር ነጋዴዎች ማረፊያ ከነበሩት የሽዋ አማራ መስመርም አዲስ አበባ ቀደሚ ናት።
የንግድ መስመሮችና ማዕከሎች እድገት በ20ኛው ምዕተ ዓመት እና የአዲስ አበባን ታሪካዊ የአማራ ባለቤትነት ከምንጩ እንመርምረው።
የሽዋ አማራ መናገሻዋ አዲስ አበባ በአማራዎች መቆርቆር የንጉሰ ነገስቱ መኖሪያ ብቻ ሳይሆን የአገሪቱ ማዕከላዊ የንግድ ማእከልና ገበያም መጀመሪያ ከነበረበት ወደ አዲስቱ ማዕከል እንዲዛወር ዋና ምክያት ሆኗል። የአዲስ አበባ ገበያም ሸቀጦች ግብይት በብዛትና በአይነት የደራበት፣ የውጭ አገር ሰዎች እንደ አገሬዎቹ ነጋዴዎች በሰፊው የሚነግዱበት ነበር። እነዚህ የውጭ አገር ነጋዴዎች ከአዲስ አበባ ውጭ ባሉ ከተሞችም የንግድ ስራቸውን በወኪሎቻቸው አማካይነት ያከናውኑ ነበር። አዲስ አበባ ማእከላዊ ገበያ መሆኗ ከደቡባዊው የአገሪቱ ክፍሎች በአማራ ክልል ታዋቂ ወደነበሩት አሮጌዎቹ ገበያዎች የሚመጣው የገበያ ሸቀጥ እንዲቀንስ አድርጓል። በተለይ ደግሞ አዲስ አበባ የፓለቲካና የኢኮኖሚ ማእከል መሆኑዋን ተከትሎ የተሰራው የአዲስ አበባ-ጅቡቲ የባቡር ሐዲድ 75 በመቶ ያክሉ ወደአገሪቱ የሚገባና ከአገሪቱ የሚወጣ ሸቀጥ መተላለፊያ በመሆኑ ፣ የጎጃም የንግድ መስመር ከሰሜንና ሰሜን ምእራብ ወደ አዲስ አበባ መተላለፊያ መሆኑ እንዲቀር ቀጥተኛ ተጽእኖ አድርጓል። በአንድ በኩል በመተማ በኩል ወደ ውጭ ከሚላኩ ምርቶች በስተቀር ከውጭ አገር ወደ ጎጃምና ጎንደር ገበያዎች የሚገቡ ልዩ ልዩ ሸቀጦች መጠን ቀንሷል።
ዳሩ ግን ወርቅ፣ የዝሆን ጥርስ፣ ዝባድ እና ቡና የመሳሰሉ ሸቀጦች ተፈላጊነታቸው በማደጉ ምክንያት የሆሮ፣ አሶሳ፣ ጊዳ፣ ቤንሻንጉል፣ ወንበራና የሌሎች የደቡብ ምእራብ አካባቢዎች ነጋዴዎች ቡሬ እየተገናኙ ሸቀጦቻቸውን በአሞሌ መለዋወጣቸው አልተቋረጠም ነበር። ስለዚህም ቡሬ በአዲስ አበባ፣ መተማና ምጽዋ ገበያዎች ከፍተኛ ተፈላጊነት ያላቸው የቆዳ፣ ሌጦ፣ ሰም፣ ቅቤ፣ በርበሬ ምርቶች መገበያያ ዋና ማእከል ነበረች። ከ1920ዎቹ በኋላ አስመራ ከበስተደቡብ በኩል ለሚመጡ ነጋዴዎች አንዳንድ ሁኔታዎችን በማመቻቸቷ፣ በእነዚህ አገልግሎቶችና በርካሽ ዋጋ በሚገዙ ጥራት ያላቸው ሸቀጦች የተማረኩ የጎጃምና የጎንደር ነጋዴዎች እስከ ኢጣሊያ ወረራ ድረስ ወደ አስመራ እየተጓዙ ይነግዱ ነበር።
በሃያኛው ክፍለ ዘመን የንግድ መስመሮች ብቻ ሳይሆኑ ወደ ውጭ በሚላኩና ወደአገር ውስጥ በሚገቡ ሸቀጦች አይነትም ላይ ለውጥ ታይቷል። በከፍተኛ መጠን ለውጭ ገበያ ተፈላጊነት የነበራቸውን የዝባድ፣ የዝሆን ጥርስና የወርቅ ምርቶች ቡና ሲተካቸው ወደ አገር ውስጥ ከሚገቡ ሸቀጦች ሁሉ ከፍተኛ ገበያ የነበረው ደግሞ አቡጀዲ ነበር። ሸቀጦችን ወደ ውጭ ገበያ በማውጣትና ከውጭ ወደ አገር ውስጥ በማስገባት ረገድ ከፍተኛ ሚና የነበራቸው የሲራራ ነጋዴዎችም ቀስ በቀስ የፈረንሳይ፣ የህንድ፣ የግሪክና የአርመን ተወላጅ በሆኑ ነጋዴዎች ተተኩ።
ከ1933 ዓም በኋላ ባለው ዘመን የነበረው ንግድ በአገር ውስጥ የተመረቱ የእርሻና የኢንዱስትሪ ውጤቶችን መግዛትና መሸጥን ያካትታል። እስከዚህ ዘመን ድረስ የነበረው የውጭና የአገር ውስጥ ንግድ ግን በአገር ውስጥ በተመረቱ ምርቶች ላይ ብቻ የተመሰረተ ነበር። የአዲስ አበባና ሌሎች ከተሞች መቆርቆር፣ የአዲስ አበባ ጅቡቲ የባቡር ሐዲድ ግንባታ በ1907 መጠናቀቅ እና በኢጣሊያ ወረራ ዘመን የመኪና መንገዶች መሰራት ለኢንዱስትሪ ማደግ ቁልፍ ሚና የተጫዎቹ ጉዳዮች መሆናቸው ይታመናል። በሌላ አገላለጽም በኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ውስጥ የኢንዱ]ስትው ዘርፍ ሚና መጫዎት የጀመረው ከነጻነት በሁዋላ ከነበረው ዘመን አንስቶ ነው። ስለዚህም በአማራ ክልል ስለኢንዱስትሪ መስፋፋት ይዞታ የምናደርገው ውይይት ኢጣሊያ ከኢትዮጵያ ከተባረረበት ዘመን ጀምሮ ይሆን ዘንድ ተገቢ ቢሆንም የንጉሰ ነገስቱና የደርግ አገዛዞች እጅግ የተማከለ የአስተዳደር ስርዓት ስለነበራቸው የኢንዱስትሪው ዘርፍ በክልሉ ንግድ ውስጥ የነበረውን ሚና የሚያሳዩ መረጃዎችን ማግኘት አልተቻለም። እነዚህ ሁለት አገዛዞች አንድ ወጥ ፖሊሲዎች መከተላቸው የንግድና የኢንዱስትሪ ስራዎች እንዳያድጉና እንዳይስፋፉ ዋንኛ ምክንያት ሆኗል።
እስከ ኢጣሊያ ወረራ ድረስ በኢትዮጵያ የነበረው የንግድ ትስስርና ልውውጥ በአማራ ህዝብ ይሁንታ የመገበያያ ገንዘብ ታትሞ በስራ ላይ በመዋሉ፣ የንግድ ፈቃድ ምስክር ወረቀት እና የዋስትና ስርዓት በመዘርጋቱ ምክንያት ወደላቀ ደረጃ ተሸጋገረ .። በኢጣሊያና በኢትዮጵያ መንግስት መንገዶች በመሰራታቸውም ነጋዴዎች ከአንዱ የኢትዮጵያ ክፍል ወደ ሌላው ተንቀሳቅሰው ለመግዛትና ለመሸጥ የተሻለ ሁኔታ ተፈጠረላቸው።
የውጭ ንግድን በተመለከተ ቀደም ባለው ዘመን ከፍተኛ ድርሻ የነበራቸው ዝባድ፣ ወርቅ፣ የዝሆን ጥርስ፣ ቅቤ፣ የቀንድ ከብቶችና ጥጥ የመሳሰሉት ሸቀጦች በቡና፣ ቆዳና ሌጦ፣ ጥራጥሬና የቅባት እህሎች ተተኩ። ቡና ለበርካታ አመታት አገሪቱ ወደ ውጭ ከምትልካቸው ምርቶች 50% እስከ 65% የሚሆነውን ሸፍኖ በመቆየቱ ምክንያት የአማራ ክልል ለአለም አቀፍ ገበያው የነበረው አስተዋጽኦ ሊያቆለቁል ችሏል። ይህም ሆኖ ግን ክልሉ ቆዳና ሌጦና እንዲሁም ጥራጥሬና የቅባት እህሎችን በማምረት ለውጭ ገበያ ሲያቀርብ ቆይቷል። ዳሩ ግን እነዚህ ምርቶች በአገሪቱ የውጭ ንግድ ውስጥ የተወሰነ ድርሻ ያላቸው በመሆኑ የውጭ ንግድ በጠቅላላው የአማራ ክልል አርሶ አደርን የገቢ ምንጭ በማሳደግ ረገድ የተጫወተው ሚና አነስተኛ ነው። እንዲያውም የእለት ፍጆታ ከፍተኛ የሆነውን ጤፍ ፣ ማር እና ቅቤ በማቅረብ የአዲስ አበባን ውበት መልሷል።
ወደአገር ውስጥ በሚገቡ ምርቶች ንግድ ረገድም ቀደም ሲል በርከት ያለ ድርሻ የነበረው ጨርቃጨርቅ መካከለኛና ከፍተኛ ዋጋ በሚያወጡ ሸቀጦች ተተክቷል። ይህም ሊሆን የቻለበት ምክንያት ወደ አገር ውስጥ በሚገቡ ሸቀጦች ዋጋ መናርና ወደውጭ በሚላኩ ጥሬ እቃዎች ዋጋ መውደቅ ሊከሰት በሚችለው የተዛባ የንግድ ሚዛን የሚደርሰውን የኢኮኖሚ ጉዳት ለመቀነስ መንግስት በተከተለው ከውጭ የሚገቡ ሸቀጦችን በአገር ምርት የመተካት ፖሊሲ አማካይነት ነው። የዚህ ፖሊሲ ውጤት፣ የጨርቃጨርቅ ውጤቶችን መጠጦችን፣ ለስላሳ መጠጦችንና ስኳርን የመሳሰሉ አላቂ የፍጆታ እቃዎችን የሚያመርቱ ኢንዱስትሪዎች ከመጠን በላይ እንዲበረክቱ አድርጓል። እነዚህ ›=ንዱስትሪዎችም በአዲስ አበባ ዙሪያ፣ የባቡር ሃዲድ በሚያቋርጣቸውና ሰፋፊ ገበያ ባለባቸው አካባቢዎች ብቻ ተከማችተው የሚገኙ ነበሩ። የአማራ ክልል ገበያዎች ደግሞ በመሰረተ ልማት አለመኖርና በየገቢ መጠን ዝቅተኛነት ምክንያት የእነዚህን ከውጭ የሚገቡ ሸቀጦችን ለመተካት የተቋቋሙ ኢንዱስትሪዎች ቀልብና ትኩረት የሚስብ ስላልነበረ ክልሉ በንጉሱ ዘመን በነበረው የተዛባ የኢንዱስትሪዎች ስርጭት ተጎጅ ሆኖ ኖሯል።
በተወሰኑ የምርት ዘርፎች ላይ የተሰማሩት እነዚህ ኢንዱስትሪዎችም በአብዛኛው በውጭ አገር ሰዎች ይዞታ ስር የነበሩ ናቸው። በኢንዱስትሪው ዘርፍ የውጭ ካፒታል በርካታውን መጠን መሸፈኑ መንግስት ከሚከተለው ለዘብተኛ ፖሊሲ የመነጨ ነበር። የውጭ ባለ ሃብቶችን ለመሳብ የንጉሰ ነገስቱ መንግስት ብር 200,000 እና ከዚያ በላይ የመነሻ ካፒታል የሚያስመዘግቡ የውጭ አገር ባለሃብቶችን ከትርፍ ከሚገኝ ገቢ ሊከፈል ከሚገባው ቀረጥ ነጻ የሚያደርግ ፖሊሲ ነበረው። ፖሊሲው በአንጻሩ ከፍተኛውን የንግድ ገቢ ቀረጥ መጠን ከተጣራ ትርፍ ላይ 15 በመቶ እንዲሆን፣ ትራክተሮችና ኬሚካሎች ቀረጥ ሳይከፈልባቸው እንዲገቡ ሲፈቅድ በአገር ውስጥ የሚመረቱ ሸቀጦችን በሚያስገቡ ላይ ደግሞ ከፍተኛ የቀረጥ ምጣኔ የሚጥል ነበር ።
አዲስ አበባ አማራው ራሱን ሰውቶ ያነገሳት ከተማ ናት። ለአማራው ልዩ ጥቅምም በአዲስ አበባ ከምክር ቤት ወንበር ጀምሮ እስከ ሰሜን ሽዋ የአማራ ክልል ዞን ልዩ ተጠቃሚነት የታሪክ ባለቤትነቱ ሊገለል አይገባም።
ኢህአዴግ በአሁኑ ውሳኔው የኦሮምያን ልዩ ጥቅም በአዲስ አበባ ለማስከበር አረቀቅኩት ያለው አዋጅ ፤ በእርግጥም እንደሚፀድቅ ተማምኖ ማቅረቡ ፤ ያልበሰለ እና ታሪካዊ የአማራን ድርሻ እና ባለቤትነት ያገለለ አሰተሳሰብ በመሆኑ ሊታረም ፣ ሊታይ እና ሌሎችም በሄሮች እና ብሄረሰቦች እንዲሁም ፣ የሽዋ አማራው በአዲስ አበባ ምክር ቤት ወንበር የመወሰን መብቱ ሊጠበቅለት ይገባል። አዲስ አበባ አማራው ራሱን ሰውቶ ያነገሳት ከተማ ናት። ለአማራው ልዩ ጥቅምም በአዲስ አበባ ከምክር ቤት ወንበር ጀምሮ እስከ ሰሜን ሽዋ የአማራ ክልል ዞን ልዩ ተጠቃሚነት የታሪክ ባለቤትነቱ ሊገለል አይገባም።
"የአማራ" መንግስት ስርዓት ውስጥ "የሸዋ አማሮች" አዲስ አበባን መርጠው ፣ ቆርቁረው ፣ አደራጅተው እና አሳድገው ለሀገር እና ለአለም ዲፕሎማሲያዊ መቀመጫነት አብቀተዋታል የ"ብሄረተኞነት"ከተማ ሳይሆን የሁሉም ብሄርች ከተማ መናገሻ አድርገዋትል። ይህ አፈታሪክ አይደለም ማንበብ ለሚችል ሰው Sorenson, Imagining Ethiopia , (New Brunswick, NJ Rutgers University Press) p.12 ወይም Messay, p.36 ፣ እና Ibid., p.23 እንዲሁም Taddesse,1972,pp 132 -135; Bahiru, p.75; Donald, C.pp.21 -22 ያገላበጠ አንባቢ ሁሉ አያጣውም። ብዙሃኑ "የሸዋ አማራ" ያቆማት እና ዙፋኑን ያፀናባትን ከተማ የአንድ ብሄር ተጠቃሚነትን ብቻ ባረጋገጠ ሁኔታ ከፖለቲካዊ ቁማርነት እየገፉ ፣ የአንድ በሄር እንብርት ናት። ሲሉ ማውራት ለኔ ትንሹ ልጅ ሲያለቅስ ትልቁን አንተ ዝም በል ብሎ የትልቁን ንብረት ቀምቶ እንደመስጠት ነው ምቆጥረው ።
አዋጁ ፍትሃዊ ማይሆነው እኩል ተጠቃሚነትን ሳይሆን የአንድ ቡድን ውቅታዊ ጥያቄ ለመመለስ ያለመ መሆኑ ላይ ማተኮሩ ነው። በእርግጥም የመንን ፣ ቀይ ባህርን ፣ ኤርትራን እና ጅቡቲን አንድም በአቅም እጥረት አልያም በፖለቲካ ድክመት እያሳለፍን ታሪካችንን ሽጠን በልተነዋል። ከታሪካዊ ባለቤትነት ይልቅ የፖለቲካ ጥቅም የሚያሸንፈው መንግስት በተፈጠረበት ጊዜ ሁሉ ብዙ ነገር ከእጃችን ወድቋል። ሀገርን መገንባት ሳይሆን ብሄርን በመገንባት በተጠመደ ስርዓት ውስጥ ደግሞ አንድን በር መዝጋት ብዙ ሽህ በሮችን እንደመክፈት ይቆጠራል ይታያልም። አዲስ አበባን መስርተው ፣ ጠቅመው ፣ የመንግስት አመራር መዋቅር ሹመው፣ አብዛኛውን የኢኮኖሚ ምንጮች አፍልቀው፣ የአዲስ አበባን የግዛት ክፍሎች ይገዙ የነበሩ፣ የአዲስ አበባ መስራች ና ፈጣሪዎች ለኢኮኖሚ እንቅስቃሴያቸው አዲስ አበባን ማዕከል አድርገው የመሰረቱ ነበሩ። የአማራ ህዝብ የሸዋ መኳንንቶች ምስጋና ይግባቸው እና የሁሉም ብሄሮች መኖሪያ አድርገዋታል።
በቅርቡ በተካሄደ ጥናትም የብሄር ማንነት የሌለው ሰፊ ህዝብ የሚኖርበት ክልል አዲስ አበባ ነው። ከ63 በመቶ በላይ የሚሆነው አማራ በሆነባት ከተማ መሬቱን የአንድ ብሄር ሃብት አድርጎ ማውጅ ምን አይነት ብስለት የጎደለው አሰራር መሆኑን ያሳያል።
ብዙሃኑ የሸዋ አማራ በድህነት እየኖረ ስልጣን አልባና እንደ አንድ ቡድን በየስርዓቱ እየተመዘበረ ባድማው ውስጥ ራሱን መፈለግ ወጋችን ፣ ታሪካችንም ነው። ይህ አዲስ አበባ ባለዎለታዋን የምትዘነጋ ከተማ አይደለችም ለእምየ ሚኒልክ ሃውልቷን ፊቱን ኦዞራ ያቆመችው በምሃል ጊዩርጊስ ወደ መንበሯ "የሸዋ አማራ ሀገር" ነው። ታዲያ እንዴት ነው በኦሮሞ የተከበበችው አዲስ አበባ ፊንፊኔ ብቻ ምትሆነው። ቋንቋዋን ምትቀይረው። የሌላው ብሄር ልጆችስ በአባታቸው ባድማ ወዴት ይወድቃሉ???
የማይመለሱ ብዙ ሽህ ጥያቄዎች ቢኖሩም ያባቶቻችንን ርስት አንሰጥም ብያለሁ እና አማራ አዲስ አበባን የሚያውቃት ማንም ከሚያውቃት በፊት ነው። Pankhurst Rassam አገላለጽ ጎንደር በ19ኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ አጋማሽ ከሰሜን፣ ከምእራብና ከደቡብ ለሚነሱ የሲራራ ነጋዴዎች ሁነኛ ማረፊያ ማዕከል ነነበረች በዚያ ዘመን ከጎንደር ወደ ማህል አገር የሲራራ ነጋዴዎች መተላለፊያ በርካታ አቅጣጫዎችና ቅርንጫፎች ነበሩት። በዚህም አንዷ አዲስ አበባ እንደነበረች በመፅሓፋቸው ከትበውታል።
ከጎንደር ሰፈራቸው የተነሱ ነጋዴዎች በጣና ሃይቅ በኩል አድርገው ወደ ይፋግ ከተሻገሩ በሁዋላ በሁለት በመከፈል አንዱ ወገን ወደምስራቅ አቅጣጫ ወደ ሸዋ (አዲስ አበባ) ሲያቀና ሌላኛው ወገን ደግሞ ወደደቡብ ወደ ጎጃም ያመራል። ወደ ደቡብ አቅጣጫ የሚዘልቀው የንግድ መስመር፣ ባሶ፣ ጉድሩ፣ በማቋረጥ ወደ ጎንደር መጥተው በጨውና ከውጭ አገር በሚገቡ እቃዎች የሚለወጡ "ወርቅ፣ የዝሆን ጥርስ፣ የከርከሮ ቀንድ፣ የግስላ/ ነብር ቆዳ፣ የጉማሬ ቆዳና ጋሻ እንዲሁም የባሮች" ምንጭ ወደሆኑት ከፋና ጃንጀሮ ይደርሳል ። ከእነዚህ በተጨማሪ ነጋዴዎች በሸዋ (አዲስ አበባ)፣ በሐረርና በዘይላ በኩል በማለፍ ወደ ሶማሌ የበርበራ ወደብ፣ "የዝሆን ጥርስ፣ ባሮችና ፈረሶች" ይዘው በመሄድ በልዋጩ ብረት፣ ጥጥና የህንድ ሸቀጦችን ለአገር ውስጥ ገበያ ያቀርቡ ነበር ።
አገር አቋራጭ ንግድ ወይም የሲራራ ንግድ በአማራ ክልል ለነበሩት በርካታ ገበያዎችና የንግድ ማእከላት መፈጠር ዋንኛ ሚና ተጫውቷል። በ18ኛውና በ19ኛው ምእተ አመታት የጎንደር ፣ የጎጃም እና የሽዋ ነጋዴዎች ምቹ መደላድል የፈጠሩባት እና ጠምደው ያረሱበት ርስታቸው ናት።
ለመሬት ባለቤትነት ታሪክ ተያይዞ የሚጠራው የንግድ መስመር ሲሆን በ19ነኛው ምእተአመት መጀመሪያ ላይ ከፍ ያለ ኢኮኖሚያዊ ጥቅም ከነበራቸው የንግድ መስመሮች የሸዋው የንግድ መስመር ነው። አጼ ሚኒልክ የመንግስታቸውን መቀመጫ ከተማ ከአንኮበር ወደ እንጦጦ ከማዘዋወራቸው በፊት አንኮበር፣ አንጎለላና አልዩ አምባ የታወቁ የገበያ ማእከላት በመሆን አገልግለዋል። በተለይ አንጎለላ ወደ ሰሜን፣ ምስራቅ፣ ምእራብና ደቡብ የሚጓዙ የአማራ፣ የኦሮሞ፣ የሶማሌ፣ የጉራጌ፣ የሐረሬና የደንከሌ ነጋዴዎችን ቀልብ የሚስብ የንግድ ማእከል ነበር።
ከሸዋ የንግድ መስመር ወደሰሜን አቅጣጫ በአድዋና በአንጣሎ አድርጎ የጎንደርና የሸዋ ሲራራ ነጋዴዎች መገናኛ ወደነበረው ምጽዋ የሚደርስ ነበር።
የጎጃም ነጋዴዎችም ወደ ሰሜን የሚያልፍ ሌላ የንግድ መስመርም ነበራቸው። ከዳንግላ ባሪያ፣ ከዘጌ ቡና ጭነው ወደ ጎንደር የሚነግዱ ነጋዴዎች በቡሬ፣ በዳንግላ ወይም ዘጌ በይስማላና በደልጊ አድርገው ወደ ጎንደር ይደርሳሉ። ከወሎና ከምስራቅ ጎጃም የሚነሱ ነጋዴዎች ደግሞ በደጀንና በብቸና በኩል አድርገው እንጦጦ ይሰፍራሉ። በሞጣ፣ አዴት፣ ወረታ አድርገው የሚጓዙት ወደ አገራቸው ወደ ደሪጣ የሚገቡት ነጋዴዎች ጭነታቸውን ደሪጣ ካላራገፉ በእንፍራዝና በምንዝሮ በኩል ተሻረው ጎንደር ይገባሉ። ወደ ታጁራ ወደብ የሚነግዱ የወሎና የአማራ ሳይንት ነጋዴዎች ደግሞ በብቸና፣ ቃሉ፣ ወረሂመኑና ደሴ አድርገው ይጓዛሉ። ንጉስ ተክለ ሃይማኖት በ1878 ዓም በእንባቦ ጦርነት በአጼ ምኒሊክ ድል እስከሆኑበት ድረስ ባሶ የደራ የንግድ ማእከል በመሆን አገልግሏል። የጎጃም የሽዋ እና የጎንደር ነጋዴዎች ማረፊያ ከነበሩት የሽዋ አማራ መስመርም አዲስ አበባ ቀደሚ ናት።
የንግድ መስመሮችና ማዕከሎች እድገት በ20ኛው ምዕተ ዓመት እና የአዲስ አበባን ታሪካዊ የአማራ ባለቤትነት ከምንጩ እንመርምረው።
የሽዋ አማራ መናገሻዋ አዲስ አበባ በአማራዎች መቆርቆር የንጉሰ ነገስቱ መኖሪያ ብቻ ሳይሆን የአገሪቱ ማዕከላዊ የንግድ ማእከልና ገበያም መጀመሪያ ከነበረበት ወደ አዲስቱ ማዕከል እንዲዛወር ዋና ምክያት ሆኗል። የአዲስ አበባ ገበያም ሸቀጦች ግብይት በብዛትና በአይነት የደራበት፣ የውጭ አገር ሰዎች እንደ አገሬዎቹ ነጋዴዎች በሰፊው የሚነግዱበት ነበር። እነዚህ የውጭ አገር ነጋዴዎች ከአዲስ አበባ ውጭ ባሉ ከተሞችም የንግድ ስራቸውን በወኪሎቻቸው አማካይነት ያከናውኑ ነበር። አዲስ አበባ ማእከላዊ ገበያ መሆኗ ከደቡባዊው የአገሪቱ ክፍሎች በአማራ ክልል ታዋቂ ወደነበሩት አሮጌዎቹ ገበያዎች የሚመጣው የገበያ ሸቀጥ እንዲቀንስ አድርጓል። በተለይ ደግሞ አዲስ አበባ የፓለቲካና የኢኮኖሚ ማእከል መሆኑዋን ተከትሎ የተሰራው የአዲስ አበባ-ጅቡቲ የባቡር ሐዲድ 75 በመቶ ያክሉ ወደአገሪቱ የሚገባና ከአገሪቱ የሚወጣ ሸቀጥ መተላለፊያ በመሆኑ ፣ የጎጃም የንግድ መስመር ከሰሜንና ሰሜን ምእራብ ወደ አዲስ አበባ መተላለፊያ መሆኑ እንዲቀር ቀጥተኛ ተጽእኖ አድርጓል። በአንድ በኩል በመተማ በኩል ወደ ውጭ ከሚላኩ ምርቶች በስተቀር ከውጭ አገር ወደ ጎጃምና ጎንደር ገበያዎች የሚገቡ ልዩ ልዩ ሸቀጦች መጠን ቀንሷል።
ዳሩ ግን ወርቅ፣ የዝሆን ጥርስ፣ ዝባድ እና ቡና የመሳሰሉ ሸቀጦች ተፈላጊነታቸው በማደጉ ምክንያት የሆሮ፣ አሶሳ፣ ጊዳ፣ ቤንሻንጉል፣ ወንበራና የሌሎች የደቡብ ምእራብ አካባቢዎች ነጋዴዎች ቡሬ እየተገናኙ ሸቀጦቻቸውን በአሞሌ መለዋወጣቸው አልተቋረጠም ነበር። ስለዚህም ቡሬ በአዲስ አበባ፣ መተማና ምጽዋ ገበያዎች ከፍተኛ ተፈላጊነት ያላቸው የቆዳ፣ ሌጦ፣ ሰም፣ ቅቤ፣ በርበሬ ምርቶች መገበያያ ዋና ማእከል ነበረች። ከ1920ዎቹ በኋላ አስመራ ከበስተደቡብ በኩል ለሚመጡ ነጋዴዎች አንዳንድ ሁኔታዎችን በማመቻቸቷ፣ በእነዚህ አገልግሎቶችና በርካሽ ዋጋ በሚገዙ ጥራት ያላቸው ሸቀጦች የተማረኩ የጎጃምና የጎንደር ነጋዴዎች እስከ ኢጣሊያ ወረራ ድረስ ወደ አስመራ እየተጓዙ ይነግዱ ነበር።
በሃያኛው ክፍለ ዘመን የንግድ መስመሮች ብቻ ሳይሆኑ ወደ ውጭ በሚላኩና ወደአገር ውስጥ በሚገቡ ሸቀጦች አይነትም ላይ ለውጥ ታይቷል። በከፍተኛ መጠን ለውጭ ገበያ ተፈላጊነት የነበራቸውን የዝባድ፣ የዝሆን ጥርስና የወርቅ ምርቶች ቡና ሲተካቸው ወደ አገር ውስጥ ከሚገቡ ሸቀጦች ሁሉ ከፍተኛ ገበያ የነበረው ደግሞ አቡጀዲ ነበር። ሸቀጦችን ወደ ውጭ ገበያ በማውጣትና ከውጭ ወደ አገር ውስጥ በማስገባት ረገድ ከፍተኛ ሚና የነበራቸው የሲራራ ነጋዴዎችም ቀስ በቀስ የፈረንሳይ፣ የህንድ፣ የግሪክና የአርመን ተወላጅ በሆኑ ነጋዴዎች ተተኩ።
ከ1933 ዓም በኋላ ባለው ዘመን የነበረው ንግድ በአገር ውስጥ የተመረቱ የእርሻና የኢንዱስትሪ ውጤቶችን መግዛትና መሸጥን ያካትታል። እስከዚህ ዘመን ድረስ የነበረው የውጭና የአገር ውስጥ ንግድ ግን በአገር ውስጥ በተመረቱ ምርቶች ላይ ብቻ የተመሰረተ ነበር። የአዲስ አበባና ሌሎች ከተሞች መቆርቆር፣ የአዲስ አበባ ጅቡቲ የባቡር ሐዲድ ግንባታ በ1907 መጠናቀቅ እና በኢጣሊያ ወረራ ዘመን የመኪና መንገዶች መሰራት ለኢንዱስትሪ ማደግ ቁልፍ ሚና የተጫዎቹ ጉዳዮች መሆናቸው ይታመናል። በሌላ አገላለጽም በኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ውስጥ የኢንዱ]ስትው ዘርፍ ሚና መጫዎት የጀመረው ከነጻነት በሁዋላ ከነበረው ዘመን አንስቶ ነው። ስለዚህም በአማራ ክልል ስለኢንዱስትሪ መስፋፋት ይዞታ የምናደርገው ውይይት ኢጣሊያ ከኢትዮጵያ ከተባረረበት ዘመን ጀምሮ ይሆን ዘንድ ተገቢ ቢሆንም የንጉሰ ነገስቱና የደርግ አገዛዞች እጅግ የተማከለ የአስተዳደር ስርዓት ስለነበራቸው የኢንዱስትሪው ዘርፍ በክልሉ ንግድ ውስጥ የነበረውን ሚና የሚያሳዩ መረጃዎችን ማግኘት አልተቻለም። እነዚህ ሁለት አገዛዞች አንድ ወጥ ፖሊሲዎች መከተላቸው የንግድና የኢንዱስትሪ ስራዎች እንዳያድጉና እንዳይስፋፉ ዋንኛ ምክንያት ሆኗል።
እስከ ኢጣሊያ ወረራ ድረስ በኢትዮጵያ የነበረው የንግድ ትስስርና ልውውጥ በአማራ ህዝብ ይሁንታ የመገበያያ ገንዘብ ታትሞ በስራ ላይ በመዋሉ፣ የንግድ ፈቃድ ምስክር ወረቀት እና የዋስትና ስርዓት በመዘርጋቱ ምክንያት ወደላቀ ደረጃ ተሸጋገረ .። በኢጣሊያና በኢትዮጵያ መንግስት መንገዶች በመሰራታቸውም ነጋዴዎች ከአንዱ የኢትዮጵያ ክፍል ወደ ሌላው ተንቀሳቅሰው ለመግዛትና ለመሸጥ የተሻለ ሁኔታ ተፈጠረላቸው።
የውጭ ንግድን በተመለከተ ቀደም ባለው ዘመን ከፍተኛ ድርሻ የነበራቸው ዝባድ፣ ወርቅ፣ የዝሆን ጥርስ፣ ቅቤ፣ የቀንድ ከብቶችና ጥጥ የመሳሰሉት ሸቀጦች በቡና፣ ቆዳና ሌጦ፣ ጥራጥሬና የቅባት እህሎች ተተኩ። ቡና ለበርካታ አመታት አገሪቱ ወደ ውጭ ከምትልካቸው ምርቶች 50% እስከ 65% የሚሆነውን ሸፍኖ በመቆየቱ ምክንያት የአማራ ክልል ለአለም አቀፍ ገበያው የነበረው አስተዋጽኦ ሊያቆለቁል ችሏል። ይህም ሆኖ ግን ክልሉ ቆዳና ሌጦና እንዲሁም ጥራጥሬና የቅባት እህሎችን በማምረት ለውጭ ገበያ ሲያቀርብ ቆይቷል። ዳሩ ግን እነዚህ ምርቶች በአገሪቱ የውጭ ንግድ ውስጥ የተወሰነ ድርሻ ያላቸው በመሆኑ የውጭ ንግድ በጠቅላላው የአማራ ክልል አርሶ አደርን የገቢ ምንጭ በማሳደግ ረገድ የተጫወተው ሚና አነስተኛ ነው። እንዲያውም የእለት ፍጆታ ከፍተኛ የሆነውን ጤፍ ፣ ማር እና ቅቤ በማቅረብ የአዲስ አበባን ውበት መልሷል።
ወደአገር ውስጥ በሚገቡ ምርቶች ንግድ ረገድም ቀደም ሲል በርከት ያለ ድርሻ የነበረው ጨርቃጨርቅ መካከለኛና ከፍተኛ ዋጋ በሚያወጡ ሸቀጦች ተተክቷል። ይህም ሊሆን የቻለበት ምክንያት ወደ አገር ውስጥ በሚገቡ ሸቀጦች ዋጋ መናርና ወደውጭ በሚላኩ ጥሬ እቃዎች ዋጋ መውደቅ ሊከሰት በሚችለው የተዛባ የንግድ ሚዛን የሚደርሰውን የኢኮኖሚ ጉዳት ለመቀነስ መንግስት በተከተለው ከውጭ የሚገቡ ሸቀጦችን በአገር ምርት የመተካት ፖሊሲ አማካይነት ነው። የዚህ ፖሊሲ ውጤት፣ የጨርቃጨርቅ ውጤቶችን መጠጦችን፣ ለስላሳ መጠጦችንና ስኳርን የመሳሰሉ አላቂ የፍጆታ እቃዎችን የሚያመርቱ ኢንዱስትሪዎች ከመጠን በላይ እንዲበረክቱ አድርጓል። እነዚህ ›=ንዱስትሪዎችም በአዲስ አበባ ዙሪያ፣ የባቡር ሃዲድ በሚያቋርጣቸውና ሰፋፊ ገበያ ባለባቸው አካባቢዎች ብቻ ተከማችተው የሚገኙ ነበሩ። የአማራ ክልል ገበያዎች ደግሞ በመሰረተ ልማት አለመኖርና በየገቢ መጠን ዝቅተኛነት ምክንያት የእነዚህን ከውጭ የሚገቡ ሸቀጦችን ለመተካት የተቋቋሙ ኢንዱስትሪዎች ቀልብና ትኩረት የሚስብ ስላልነበረ ክልሉ በንጉሱ ዘመን በነበረው የተዛባ የኢንዱስትሪዎች ስርጭት ተጎጅ ሆኖ ኖሯል።
በተወሰኑ የምርት ዘርፎች ላይ የተሰማሩት እነዚህ ኢንዱስትሪዎችም በአብዛኛው በውጭ አገር ሰዎች ይዞታ ስር የነበሩ ናቸው። በኢንዱስትሪው ዘርፍ የውጭ ካፒታል በርካታውን መጠን መሸፈኑ መንግስት ከሚከተለው ለዘብተኛ ፖሊሲ የመነጨ ነበር። የውጭ ባለ ሃብቶችን ለመሳብ የንጉሰ ነገስቱ መንግስት ብር 200,000 እና ከዚያ በላይ የመነሻ ካፒታል የሚያስመዘግቡ የውጭ አገር ባለሃብቶችን ከትርፍ ከሚገኝ ገቢ ሊከፈል ከሚገባው ቀረጥ ነጻ የሚያደርግ ፖሊሲ ነበረው። ፖሊሲው በአንጻሩ ከፍተኛውን የንግድ ገቢ ቀረጥ መጠን ከተጣራ ትርፍ ላይ 15 በመቶ እንዲሆን፣ ትራክተሮችና ኬሚካሎች ቀረጥ ሳይከፈልባቸው እንዲገቡ ሲፈቅድ በአገር ውስጥ የሚመረቱ ሸቀጦችን በሚያስገቡ ላይ ደግሞ ከፍተኛ የቀረጥ ምጣኔ የሚጥል ነበር ።
አዲስ አበባ አማራው ራሱን ሰውቶ ያነገሳት ከተማ ናት። ለአማራው ልዩ ጥቅምም በአዲስ አበባ ከምክር ቤት ወንበር ጀምሮ እስከ ሰሜን ሽዋ የአማራ ክልል ዞን ልዩ ተጠቃሚነት የታሪክ ባለቤትነቱ ሊገለል አይገባም።
0 comments