Open top menu
October 17, 2020
የገዳ ሥርዓት [ክፍል ፩]  - ( Achamyeleh Tamiru )

የገዳ ሥርዓት [ክፍል ፩]

( Achamyeleh Tamiru ) -

የኦሮሞ ብሔርተኞች ኦሮሞ ያልሆነውን ኢትዮጵያዊ ዲና [ጠላት] እያሉ ጥላቻ በማስተማር ባሳደጉት የቄሮ ትውልድ ጭካኔና አውሬነት የረኩ አይመስልም። ይህም በመሆኑ አውሬ ካደረጓቸው የኦሮሞ ቄሮዎች አልፈው የአዲስ አበባ ልጆችም ገዳ የሚባለውን ኋላቀር የወረራና ወታደራዊ ሥርዓት እንዲያውቁና ወደ አረመኔነት እንዲመለሱ ለማድረግ መዘጋጀታቸውን ነግረውናል።

የገዳ ሥርዓት የኦሮሞ የገዢ መደብ ኢትዮጵያን ሲወር ከ28 በላይ ጥንታዊ የኢትዮጵያ ቋንቋዎችን፣ ነገዶችን፣ ማንነቶችንና ባሕሎችን በተሳከ ሁኔታ ያጠፋበት ወታደራዊ ሥርዓት ነው። የገዳ ሥርዓት በኦነጋውያንና ደቂቆቻቸው እንደሚደሰኮረው እንኳን ዲሞክራሲያዊ ስርዓት ሊሆን ቀርቶ የፖለቲካ ስርዓት እንኳን አልነበረም። የገዳ ሥርዓት የአርመኔነት ጥግ የታየበት ወታደራዊ ሥርዓት ነበር። ይህን የምለው ፈጥሬ ሳይሆን ከዋናው የገዳ ታሪክ መዝጋቢ ከአባ ባሕርይ መጽሐፍ በተጨማሪ አባ ባሕርይ የጻፉትን ታሪክ ዝቀው የመመረቂያ ወረቀቶቻቸውን ካሰናዱት ከኦሮሞ ብሔርተኞቹ ከፕሮፈሰር መሐመድ ሐሰን፣ ከፕሮፈሰር ሕዝቃኤል ጊቢሳ፣ ከፕሮፌሰር ተሰማ ጠአ፣ ወዘተ ጽሑፎች ሳነብ ያገኘሁትን ታሪክ መሰረት በማድረግ ነው።

የገዳ ሥርዓት ከሌሎች ወታደራዊ ሥርዓቶች የሚለየው በምርኮኞች ላይ ሳይቀር ritualized የሆነው culture of violenceን ተቋማዊ ማድረጉ ነው። ሌሎች ወታደራዊ ሥርዓቶች ሰላማዊ ሰው አይገድሉም፤ ተፋላሚ ጠላት እንኳ ቢሆን የምርኮ አያያዝ ሥርዓት አላማቸው። የገዳ ሥርዓት ግን ተቀዳሚ ኢላማው የታጠቀ ተፋላሚ ኃይል ሳይሆን አገር አማን ብሎ የተቀመጠ ሰላማዊ ሕዝብ ነው። በገዳ ሥርዓት አንድ ሰው ለግድያ ከመሰማራቱ በፊት ለወኔው ማነሳሻ ብዙ ደም ይጠጣል፡፡ ከዚያም አገር አማን ነው ብሎ የሚሄደን መንገደኛ ወይም በቤቱ የተቀመጠን ሰላማዊ ሰው አድብቶ በመግደል ወንድ ከሆኑ ብልቱን፤ ሴት ከሆነች ደግሞ ጡቷን ቆርጦ ወደ ጎጆው ይመለሳል፡፡ ሲመለስ ፉከራ ያሰማል፡፡ እንዲሁም ሰልቦ የገደለውን ሰው ያሰማውን የጣእር ድምጽ አስመስሎ በመጮህ ያፌዛል፡፡ አንድ የኦሮሞ ወንድ ይህንን ማድረግ ከቻለ ብቻ ነው በጆሮው ላይ የብር ሎቲ ማንጠልጠል የሚፈቀድለት ወይም በግንባሩ ላይ ከለቻ የሚያስረው።

በቡታ በዓል ሰው ገድሎ መመለስ ያልቻለ ኦሮሞ ውርደት ይከናነባል፤ በግንባሩ ላይ ምልክት ይደረግበትና ወንድ አለመሆኑ ለማሳየት በትንሽ እቃ ወተት ተሰጥቶት ቅቤ እስኪወጣ ድረስ እንዲገፋው ይደረጋል። አንድ ኦሮሞ ሰው ካልገደለ በቀር በገዳ ሥርዓት ውስጥ ቦታ አይኖረውም፡፡ [ Huntigford, G. W. (1955). The Galla of Ethiopia: The kingdoms of Kafa and Janjero, Page 64]

ብቸኛው የገዳ ታሪክ ምንጭ አባ ባሕርይ ምስጋና ይግባቸውና የገዳ ሥርዓትን ከእድሜ ደረጃ አወጣጥ ጀምሮ እያንዳንዱ የሥርዓቱ ደንቦች የተቃኙት ወታደራዊ የበላይነትን ለማስገኘት እንደሆነ አስገንዝበውናል። በገዳ ሥርዓት መሪ ሆኖ የሚመረጠው ሰው ከእድሜ አቻዎቹ ብዙ ሰው የገደለው ነው። ከመመረጡ በፊት ሰውን አድኖ ገድሎ ለመረጃነት ይዞ ያልተገኘ ኦሮሞ በገዳ ሥርዓት አይመረጥም። በገዳ ሥርዓት አንዱ ሉባ ከጓደኞቹ መካከል በልጦ ለመገኘት በተለይ ወንዶችን፣ በእናት ማኅጸን ውስጥ ያለ ሕጻንን ጨምሮ ገድሎ ቸብቸቦውን ይዞ መቅረብ የሥርዓቱ አንድ አካል ነው። ባጭሩ የገዳ ስርዓት የገዳዮች ስርዓት ነው።

የገዳ ሥርዓት ምንም ዓይነት የዲሞክራሲ መልክ እንዳልነበረው የሚያሳየው ሌላው አቋሙ የፖለቲካ ስርዓቱ መሪ (አባ ቦኩ) በቤተሰብ ተወራራሽ ወይም ከልጅ ልጅ የሚያልፍ መሆኑ ነው። እውነተኛው ኦሮሞ ምንም እንኳን በቁጥር ትንሽ[ከአስር እንድ] ቢሆንም ወታደራዊ የበላይነትን እንዲያገኝ ያደረገው ይህ ለጦርነት የሰላው አደረጃጀቱ ግን ቁጥሩ እንዲበዛ አድርጎታል። አባ ቦኩ (የፖለቲካ ቢሮው) ከልጅ ልጅ የሚተላለፍ በመሆኑ ተቋማዊ ትውፊቱን (institutional memory) ሲያስቀጥል የወታደራዊ ክንፉ የሚሞላው በጉልበትም፣ በእድሜም የመግደል ችሎታቸው ከፍተኛ በሆኑ መሪዎች ነበር። ይህ በሌሎች የኢትዮጵያ ማኅበረሰቦች ከነበረው ከቤተሰብ ወደ ቤተሰብ ከሚተላለፈው የስልጣን ሽግግር ሙሉ በሙሉ የተለየ ነበር።

ሞጋሳ የገዳ ሥርዓት ምሰሶ ነው። የሞጋሳ ሥርዓት የተጀመረው እውነተኛ ኦሮሞ የሆኑት የቦረናና ባሬንቱ ነገዶች ወረራ ሲጀምሩ የሚወሩት ግዛት እያሰፋ በመሄዱ ቁጥራቸው ሳስቶ ለጥቃት ተጋላጭ እንዳይሆኑ ነበር። በዚህ ጊዜ የወረሩትን አካባቢ ሙሉ በሙሉ ከመግደል የማረኩትን ባሪያ፣ ገባርና ገርባ ቢያደጉት የበለጠ ጠቀሜታ እንዳለው ተረድተው የመጀመሪያ ልምዳቸውን ሻሽለውታል። በዚህ ጊዜ ነበር የጉዲፈቻና ሞጋሳ ሥርዓቶች በስራ ላይ መዋል የጀመሩት። ቦረናና ባሬንቱ ሲስፋፉ በጦርነት የያዙትን ሕዝብ ገድለው ከመጨረስ ይልቅ ባሕሉንና ቋንቋውን በማጥፋት፣ በምንም ዓይነት ማንነቱን ወደ ኋላ እንዳያስታውስ አድርገው የአባቱን ስም ሳይቀር በመቀየር ለጦርነቱ የሚማገድ ኃይል ለማድረግ ነበር ሞጋሳ የተጀመረው። እንዲህም ከተደረገ በኋላ በሞጋሳ የተያዘው ኦሮሞ አልተደረገም ገርባ እንጂ። ገርባ አገልጋይ ብቻ ሳይሆን ኦሮሞው በፈለገ ጊዜ የሚሸጠው ባሪያም ነበር። ለዚህ ምንጭ የኦሮሞ ብሔርተኛው ፕሮፈሰር መሐመድ ሐሰን ከሰላሳ ዓመታት በፊት “The Oromo of Ethiopia: A History, 1570-1860” በሚል ባሳተመው መጽሐፍ ገጽ 126 ላይ የጻፈውን ያነቧል።

የሞጋሳ ስሪት ከልጅ ልጅ የሚተላለፍ ሥርዓት ነበር። በገዳ ሥርዓት መሰረት ገርባ የተደረገው ሕዝብ ማንነቱን እንዲያጣ ተደርጎ፤ ከማኅበራዊ ቦታውም ወጥቶ መሬትም ሆነ ሌላ ንብረት እንዳያፈራ ይከለክላል። ገርባ የኦሮሞ ንብረት ብቻ ነበር። ባጭሩ ገርባ ምንም እንኳን ኦሮምኛ እንዲናገር ቢገደድም ኦሮሞ ግን ፈጽሞ አልነበረም፤ እንዲሆንም የገዳ ሥርዓትም አይፈቅድለትም።

ከ17ኛው እስከ 20ኛው መቶ ክፍለ ድረስ አብዛኛው የባሪያ አቅራቢዎች ሞቲ[የኦሮሞ ንጉሥ] የሆኑት አንጋፋዎች እንደነበሩ የተመዘገበ ታሪክ ነው። በዚህም የተነሳ አብዛኛው ባሪያ ኦሮምኛ ተናጋሪ ነበር። ይህ ማለት ግን ሞቲዎች ለሽያጭ የሚያቀርቡት ኦሮሞዎችን ነበር ማለት አይደለም። በሞቲዎችና አባገዳዎች ለሽያጭ የሚቀርቡት አገልጋይ የነበሩ ገርባዎች ነበሩ። በደቡቡ፣ በምዕራቡና በመካከለኛው የኢትዮጵያ ክፍል ከአባገዳ መር የዘር ጀኖሳይድ የተረፉት ነገዶች እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ በሞቲ ባሪያ ፈንጋዮች ጥቃትን ያስተናግዱ ነበር። ለዚህ የሚከተሉትን እውነታዎች መጥቀስ ይቻላል።

ዳግማዊ አባ ጅፋርን በ1904 ዓ.ም. በሚኖሩበት ጅማ ሄዶ የጎበኛቸው ፊታውራሪ ተክለ ሐዋርያት ተክለ ማርያም አባ ጅፋር «ከአንድ ሚሊዮን በላይ የአካባቢውን ሕዝብ በተለይም የሞችን በባርነት ሽጦ እንደጨረሰው» ኦቶባዮግራፊ [የሕይወቴ ታሪክ] በሚል ባዘጋጁት የታሪክ መጽሐፍ ውስጥ አስፍረዋል።

Achamyeleh Tamiru, [16.10.20 03:10]
በ1916 ዓ.ም. ኢትዮጵያ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት [League of Nations] አባል ለመሆን ባመለከተችበት ወቅት በእንግሊዝ መንግሥት ከፍተኛ ተቃውሞ ቀርቦባት ነበር። የኢትዮጵያን መንግሥት የአባልነት ማመልከቻ ለተባበሩት መንግሥታት ድርጅት [League of Nations] ለማስገባት ወደ ጀኔቫ የተላከው ቡድን መሪ የነበሩት ራስ ናደው አባ ወሎ በፈረስ ስማቸው «አባ መብረቅ» እንግሊዝ ኢትዮጵያ የመንግሥታቱ ማኅበር አባል እንዳትሆን የተቃወመችበትን ምክንያት ለንግሥተ ነገሥታት ዘውዲቱ በላኩት የቴሌግራም መልዕክት፤

«እንግሊዝ ዓለም አቀፍ የመገናኛ ብዙሐን የዘገቡትንና በሱዳን፣ በኬንያ፣ በኤደንና በግብጽ ባሉት የቅኝ ግዛት መንግሥቱ በኩል የሰበሰበውን ማስረጃ በማያያዝ በደቡብ ኢትዮጵያ እየተካሄደ ስለነበረው የባርያ ንግድ ሁኔታ፤ በተለይም የጂማው አባ ጅፋር በከፋ፣ በማጂ፣ በጊሚራና በጉራፈርዳ ሕዝብ ላይ እየካሄዱት ያለው መጠነ ሰፊ የባሪያ ንግድ ለማኅበሩ የፖለቲካ ኮሚሲዮንና ለጠቅላላ ጉባኤ በማቅረብ አባል እንዳንሆን ከፍተኛ ተቃውሞ አቅርቦብናል»

ሲሉ አስረድተዋል።

ሆኖም ግን ኢትዮጵያ ውስጥ በአባ ጅፋር አማካኝነት የሚካሄደው የባርያ ንግድ ባጭር ጊዜ ውስጥ ጨርሶ እንዲታገድና የሰው ልጅ መብት በመላው የአገሪቱ ግዛት እንዲከበር የአልጋወራሽ ተፈሪ መንግሥት ለመንግሥታቱ ማኅበር ቃል በመግባት ኢትዮጵያ ያቀረበችው የአባልነት ጥያቄ ተቀባይነት አግኝቶ ከመስከረም 17 ቀን 1916 ዓ.ም. ጀምሮ ኢትዮጵያ የመንግስታቱ ማህበር 57ኛ አባል ሆና መመዝገቧ በይፋ ታወጀላት።

ባጭሩ በአባ ገዳ የተመራው የኦሮሞ ገዢ መደብ ወረራ ተሳክቶለት ኢትዮጵያን ሙሉ በሙሉ ቢቆጣጠር ኖሮ ሁሉም ባሕልና ቋንቋ ተጨፍልቆና ተሰልቅጦ ዛሬ ሁሉም አንድ ወጥ ኦሮሞ ብቻ ይሆን ነበር። ለዚህ ማሳያው ቀላል ነው። ኦሮሞ በወረራ የያዛቸው የጥንት ነገዶች ሙሉ በሙሉ ወደ ኦሮሞነት ተቀይረዋል። ኦሮሚያ በሚባለው ክልል ውስጥ ከኦሮሞ ወረራ በፊት ይኖሩ የነበሩት ጥንታዊ ነገዶች ሁሉ ጸድተው ማንነታቸውን እንዲቀይሩ ተገድደዋል። ይህም የሆነው በዋናነት በገዳ ሥርዓ ነው። እንደ መልካም ነገር የአዲስ አበባ ልጆች እንዲማሩት እየተፈለገ ያለው ይህንን ጥንታዊ የኢትዮጵያ ነገዶች የጸዱበትን ሥርዓት ነው።

ገራሚው ነገር ዛሬ ገዳን ለሌላው ሊያስተምሩ የተነሱት ባለጊዜዎች «ተበደልን፣ የዘር ጥቃት ደረሰብን» ብለው ሊያለቃቅሱ የነበሩና በጦረኛ አባገዳዎች ተሸንፈው የተያዙ ገርባ ልጆች መሆናቸው ነው። እነዚህ ገርባዎች ዳግማዊ ዐፄ ምኒልክ ተነስተው አባ ላፋዎች [የኦሮሞ የመሬት ከበርቴዎች]፣ ሞቲዎች፣ መልከኞች [የአካባቢ ገዢዎች]፣ አባ ገዳዎች ወዘተ ጠቅልለው ከያዙት መሬት ውስጥ ቀንሰው የሚያርሱት መሬትና የግል ንብረት ባለቤት እስኪያደርጓቸው ድረስ መሬትም ንብረትም እንዳልነበራቸው አያውቁም። ይህን ባለማወቃቸው ዛሬ በኦነጋውያን በየአካባቢው የሚደርሰውን ጥቃትና ተዳፍኖ የቆየው ከሀያ ስምንት በላይ የኢትዮጵያ ነገዶች በሞጋሳ የጠፉበት የገዳ ሥርዓት የወለደውን ጦረኝነት ክፍል ሁለት ለማስቀጠም ገዳን ሊያስተምሩ ይዳዳቸዋል።


ኢትዮጵያ የተወረረችበትን፣ ነባር ነገዶቿ ከርስታቸው የፈለሱበትን፣ 400 ዓመታት ሙሉ በደም ጎርፍ የታጠብንበትን፣ ከ28 በላይ የኢትዮጵያ የጥንት ነገዶች ለወሬ ነጋሪ ሳይተርፍ የጠፉበትን የገዳን ሥርዓት ከጥፋቱ ለተረፉት ማስተማር ስድስት ሚልዮን አይሁዶችን ለጥፋት የዳረገውን የናዚ ሥርዓት ለእብራውያን ልጆች ከማስተማር ተለይቶ አይታይም። የናዚዎቹን ስኬት ለማስተማር የሚፈልጉ የሉም ማለት አይደለም። በደንብ አሉ። ሆኖም ግን ታሪክ በትክክል በመነገሩ ጨካኝ የናዚ ሥርዓት በዓለም ላይ እየተወገዘ እንዲኖርና ተመልሶ እንዳይመጣ ተደርጓል። በአገራችን ግን ታሪካችንን በደምብ ባለማወቃችን፣ የዘር ማጥፋትን የተካሄደበትና ከሀያ ስምንት በላይ የኢትዮጵያ ነገዶች የጠፉበትን ገዳን እንደበረከት እንድንማረው እየተደረግን እንገኛለን። ታሪካችንን ጠንቅቀን ያወቅን ቢሆን ኖሮ የጠፋንበትን ወታደራዊና የወረራ ሥርዓታቸውን እንድንማር ሳይሆን በወረራ በያዙት ባድማ ላይ የነባሩን ሕዝብ ቋንቋ፣ ባሕልና ሃይማኖት አጥፍተው የሰፈሩት የሥርዓቱ ባለቤቶች የሆኑት አባገዳዎች ቋንቋና ባሕላቸውን ላጠፉባቸው፣ መሬታቸውን ነጥቀው ገርባ ላደረጓቸው፣ ባሪያ አደርገው ለሸጧቸው ከሀያ ስምንት በላይ የኢትዮጵያ ነገዶች በይፋ ይቅርታ እንዲጠይቁ ማድረግ እንችል ነበር።

Achamyeleh Tamiru, [16.10.20 03:16]
[ Photo ]

Achamyeleh Tamiru, [16.10.20 13:33]
ኦሮሞን ባርያ አድርጎ የሸጠው ባርያ ፈንጋይ ማን ነበር?

የኦሮሞ ብሔርተኛው ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን በጃዋር መሐመድ ቴሌቭዥን ቀርቦ “በዲሞክራሲያዊነቱ ወደር የለውም በሚሉት የገዳ ሥርዓት ላይ በመሰንዘር ላይ የሚገኙ ጥቃቶች” ያላቸውን ትችቶች ለመከላከል ሞክሯል። ሆኖም ግን በዘመኑ በተመዘገበ፤ በቀዳሚ የታሪክ ማስረጃ ላይ ተመስርተን የዘር ማጥፋትና የወረራ ወታደራዊ ሥርዓት ስለሆነው ስለ ገዳ የሰነዘርነውን ትችት እንደ ታሪክ ባለሞያ እንዱንም እንኳ በማስረጃ ላይ ተመስርቶ ሳይከላከል እሱና ሌሎች የኦሮሞ ብሔርተኞች ስለ ገዳ ድርጅት የፈጠሩትን ፕሮፓጋንዳ ብቻ አስተጋብቶ ከቴሌቭዥኑ መስኮት ወርዷል።

አስተርጉሜ በሰማሁት ዲስኩሩ ውስጥ ያስተጋባው አንዱ የፈጠራ ትርክቱ ግን ሳያስገርመኝ አልቀረም። የገዳ ድርጅትን እውነተኛ ታሪክ የምናቀርብ ሰዎችን “ኦሮሞን ባርያ አድርገው ይሸጡ የነበሩ ነፍጠኛ ልጆች በሰዎች እኩልነት የሚያምነውን የገዳ ሥርዓት የባርያ አሳዳሪዎች ሥርዓት አድርገው የመተቸት የሞራል ልዕልና የላቸውም” ሲል ደፋር ንግግር አድርጓል። ይገርማል! ጤና ይስጥልኝ ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን ማነው ኦሮሞን ባርያ አድርጎ የሸጠው? እስቲ ዶሴው ይውጣና ይመርመር።

ኦሮሞን ፈንግሎ ማን ባርያ አድርጎ እንደሸጠው የሚያሳይ የታሪክ ማስረጃ ስናፈላልግ ፕሮፈሰር ሳንድራ ሼል የተባሉ የታሪክ ምሑር “Children of Hope፡ The Odyssey of the Oromo Slaves from Ethiopia to South Africa በሚል በቅርቡ ያሳተሙትን ጥናት እናገኛለን።

ከታች የታተሙት ሁለት ጥናታዊ መግለጫዎች ዛሬ ኦሮምያ ክልል ከሚባለ አካባቢ በባርያ ነጋዴዎች ተፈንግለው ወደ ደቡብ አፍሪካ የተሸጡ የኦሮሞ ልጆችን ማን ፈንግሎ እንደሸጣቸው የሚያሳዩ የፕሮፈሰር ሳንድራ ሼል ጥናት ውጤቶች ናቸው። ወደ ደቡብ አፍሪካ የተሸጡ የኦሮሞ ልጆችን ማን ፈንግሎ እንደሸጣቸው የሚያሳየው ይህ የፕሮፈሰር ሳንድራ ሼል የጥናት ውጤት የሚገኘው ፕሮፈሰሯ “Children of Hope፡ The Odyssey of the Oromo Slaves from Ethiopia to South Africa” በሚል ርዕስ አዘጋጅተው በኦሀዮ ዩኒቨርሲቲ ፕሬስ ባሳተሙት መጽሐፋቸው ከገጽ 65 እና 66 ነው። ፕሮፈሰር ሳንድራ የኦሮሞ ልጆችን ማን ፈንግሎ እንደሸጣቸው ያጠኑት ተፈንጋዮቹ የኦሮሞ ልጆች ራሳቸው ከሰጡት የራስ ምስክር ነው። ጥናቱ የሚያጠቃልለው እስከ 1882 ዓ.ም. ድረስ የተፈነገሉትን በመቶዎች የሚዎጠሩ የኦሮሞ ወንድና ሴት ልጆችን ነው።

ከታች በታተመው ጥናት መሰረት 35 ፐርሰንቱ የኦሮሞ ልጆች በኦሮሞ ተወላጆች እንደተፈነገሉና ባርያ ተደርገው እንደተሸጡ ተናግረዋል። 23 ፐርሰንቱ ደግሞ በሲዳማ ተወላጅ ፈንጋዮች እንደተሸጡ ቃላቸውን ሰጥተዋል። የተቀሩት ተፈንጋዮች ከተለያዩ የኢትዮጵያ ነገዶች በተወለዱ ባርያ ነጋዴዎች እንደተፈነገሉ ተናግረዋል።

በጥናቱ የተካተቱ በባሪያ ነጋዴዎች የተፈነገሉ የኦሮሞ ሁሉ በሰጡት የቃል መሰረት ግን አንድም የአማራ ተወላጅ የሆነ ሰው በመፈንገል ባርያ አድርጎ እንደሸጣቸው የሚያሳይና ማስረጃ ሆኖ ሊቀርብ የሚችል የአንድም ተፈንጋይ እንኳን የቃል ምስክር የለም። ተፈንጋዮቹ የኦሮሞ ልጆች ራሳቸው በሰጡት የቃል ምስክር ባብዛኛው የፈነገላቸው የኦሮሞ ተወላጅ ባርያ ነጋዴ መሆኑን በተናገሩበት ሁኔታ፤ አንድም የአማራ ተወላጅ ፈንግሎ እንደሸጠ እንዳቸውም ተፈንጋዮች ባልተናገሩበት ሁኔታ ነው እንግዲህ “የታሪክ ምሑሩ” ፕሮፈሰር መሐመድ ሐሰን ያለ አንዳች ማስረጃ በጥላቻና በጨበጣ አማራን በባሪያ ሻጭነት የሚከሰው። በታሪክ ተመዝግቦ የምናገኘው እውነትና ተፈንጋዮቹ የኦሮሞ ልጆች ራሳቸው በሰጡት የታሪክ ምስክር መሰረት ግን ኦሮሞን ፈንግሎ ባርያ አድርገው የሸጠው ጎረቤቱ የኦሮሞ ተወላጅ የሆነ ማርያ ፈንጋይ መሆናቸው ነው።

ፕሮፈሰር ሳንድራ ሼል በጥናታቸው የሚነግሩን ሌላም አስዳማሚ የታሪክ እውነት አለ። የኦሮሞ ተወላጅ ባርያ ፈንጋዮች ባሪያ አድርገው የሸጧቸውን የአሮሞ ልጆች ዳግማዊ ዐፄ ምኒልክ ደቡብ አፍሪካ ድረስ በመላላክ ገንዘብ ጭምር እየከፈሉ ነጻ እንዲወጡና ወደ አገራቸው እንዲመለሱ ማድረጋቸውን ይነግሩናል። ከነዚህ በኦሮሞ ተወላጆች ወደ ደቡብ አፍሪካ ከተሸጡት ባሮች መካከልም ዳግማዊ ዐፄ ምኒልክ ገንዘብ ከፍለው ነጻ ያወጡት ያንዱ ሰው ትውልዶች በማውሳት በደርግ ዘመን ከኢትዮጵያ ወደ ካናዳ ተሰደው አሁንም ድረስ ካናዳ ውስጥ እንደሚኖሩ ነግረውናል። የተዘመገው የታሪክ እውነት ይህ ሆኖ ሳለ ነው እንግዲህ ፕሮፈሰር መሐመድ ሐሰን ሳያፍር የኦሮሞ ተወላጆች የሰጧቸውን የኦሮሞ ባሮች ገንዘብ ከፍለው ነጻ ያወጧቸውን የዐፄ ምኒልክ ልጆች “ኦሮሞን ባርያ አድርገው ይሸጡ የነበሩ ነፍጠኛ ልጆች የገዳ ሥርዓትን የባርያ አሳዳሪዎች ሥርዓት አድርገው የመተቸት የሞራል ልዕልና የላቸውም” የሚለው።

በስተመጨረሻም ሳይመረምሩ እነ ፕሮፈሰር መሐመድ ሐሰን ያራገፉባቸውን የአህይነት ጭነት ተሸክመው እየዞሩ አማራን በባርያ ፈንጋይነት የሚከሱ የኦሮሞ ብሔርተኞችንና ደጋሚዎቻቸውን «ወሬ ሲነግሩህ ሀሳብ ጨምርበት» የሚለውን የአያቶቻችን ጥልቅ ምክርና ታላቁ ጥላሁን ገሰሰ «አመልካች ጣት» በሚል በተጫወተው ዘፈን ውስጥ፤

ባንዷ ስትጠቁም ከጣቶችህ መሀል፣
ሶስቱ ግን ራስህን ይመለከቱሀል፤
በሚል ያቀነቀነውን ግጥም በመለገስ ልሰናበት!
_____
ከስር የታተመውን Oromo Man with Berta Slave የሚል መግለጫ ያለውን ታሪካዊ ፎቶ የገኘሁት ወለጋ ውስጥ ወንጌል ሲስብክ የኖረው ወንጌላዊው John G. Hall "Ethiopia in the Modern World (Explorations of Africa)" በሚል ርዕስ እ.ኤ.አ. በ2002 ካሳተመው መጽሐፍ ከገጽ 50 ላይ ነው። ሁለተኛው ፎቶ በጀርመንኛ የተጻፈው መግለጫ ያለው ሲሆን መግለጫው ወደ እንግሊዝኛ ሲተረጎም Galla Man with Sidama slave የሚል ይሆናል።



 



 

 

 

Read more
የገዳ ሥርዓት [ክፍል ፩]  ( Achamyeleh Tamiru )

የገዳ ሥርዓት [ክፍል ፩]

( Achamyeleh Tamiru ) -

የኦሮሞ ብሔርተኞች ኦሮሞ ያልሆነውን ኢትዮጵያዊ ዲና [ጠላት] እያሉ ጥላቻ በማስተማር ባሳደጉት የቄሮ ትውልድ ጭካኔና አውሬነት የረኩ አይመስልም። ይህም በመሆኑ አውሬ ካደረጓቸው የኦሮሞ ቄሮዎች አልፈው የአዲስ አበባ ልጆችም ገዳ የሚባለውን ኋላቀር የወረራና ወታደራዊ ሥርዓት እንዲያውቁና ወደ አረመኔነት እንዲመለሱ ለማድረግ መዘጋጀታቸውን ነግረውናል።

የገዳ ሥርዓት የኦሮሞ የገዢ መደብ ኢትዮጵያን ሲወር ከ28 በላይ ጥንታዊ የኢትዮጵያ ቋንቋዎችን፣ ነገዶችን፣ ማንነቶችንና ባሕሎችን በተሳከ ሁኔታ ያጠፋበት ወታደራዊ ሥርዓት ነው። የገዳ ሥርዓት በኦነጋውያንና ደቂቆቻቸው እንደሚደሰኮረው እንኳን ዲሞክራሲያዊ ስርዓት ሊሆን ቀርቶ የፖለቲካ ስርዓት እንኳን አልነበረም። የገዳ ሥርዓት የአርመኔነት ጥግ የታየበት ወታደራዊ ሥርዓት ነበር። ይህን የምለው ፈጥሬ ሳይሆን ከዋናው የገዳ ታሪክ መዝጋቢ ከአባ ባሕርይ መጽሐፍ በተጨማሪ አባ ባሕርይ የጻፉትን ታሪክ ዝቀው የመመረቂያ ወረቀቶቻቸውን ካሰናዱት ከኦሮሞ ብሔርተኞቹ ከፕሮፈሰር መሐመድ ሐሰን፣ ከፕሮፈሰር ሕዝቃኤል ጊቢሳ፣ ከፕሮፌሰር ተሰማ ጠአ፣ ወዘተ ጽሑፎች ሳነብ ያገኘሁትን ታሪክ መሰረት በማድረግ ነው።

የገዳ ሥርዓት ከሌሎች ወታደራዊ ሥርዓቶች የሚለየው በምርኮኞች ላይ ሳይቀር ritualized የሆነው culture of violenceን ተቋማዊ ማድረጉ ነው። ሌሎች ወታደራዊ ሥርዓቶች ሰላማዊ ሰው አይገድሉም፤ ተፋላሚ ጠላት እንኳ ቢሆን የምርኮ አያያዝ ሥርዓት አላማቸው። የገዳ ሥርዓት ግን ተቀዳሚ ኢላማው የታጠቀ ተፋላሚ ኃይል ሳይሆን አገር አማን ብሎ የተቀመጠ ሰላማዊ ሕዝብ ነው። በገዳ ሥርዓት አንድ ሰው ለግድያ ከመሰማራቱ በፊት ለወኔው ማነሳሻ ብዙ ደም ይጠጣል፡፡ ከዚያም አገር አማን ነው ብሎ የሚሄደን መንገደኛ ወይም በቤቱ የተቀመጠን ሰላማዊ ሰው አድብቶ በመግደል ወንድ ከሆኑ ብልቱን፤ ሴት ከሆነች ደግሞ ጡቷን ቆርጦ ወደ ጎጆው ይመለሳል፡፡ ሲመለስ ፉከራ ያሰማል፡፡ እንዲሁም ሰልቦ የገደለውን ሰው ያሰማውን የጣእር ድምጽ አስመስሎ በመጮህ ያፌዛል፡፡ አንድ የኦሮሞ ወንድ ይህንን ማድረግ ከቻለ ብቻ ነው በጆሮው ላይ የብር ሎቲ ማንጠልጠል የሚፈቀድለት ወይም በግንባሩ ላይ ከለቻ የሚያስረው።

በቡታ በዓል ሰው ገድሎ መመለስ ያልቻለ ኦሮሞ ውርደት ይከናነባል፤ በግንባሩ ላይ ምልክት ይደረግበትና ወንድ አለመሆኑ ለማሳየት በትንሽ እቃ ወተት ተሰጥቶት ቅቤ እስኪወጣ ድረስ እንዲገፋው ይደረጋል። አንድ ኦሮሞ ሰው ካልገደለ በቀር በገዳ ሥርዓት ውስጥ ቦታ አይኖረውም፡፡ [ Huntigford, G. W. (1955). The Galla of Ethiopia: The kingdoms of Kafa and Janjero, Page 64]

ብቸኛው የገዳ ታሪክ ምንጭ አባ ባሕርይ ምስጋና ይግባቸውና የገዳ ሥርዓትን ከእድሜ ደረጃ አወጣጥ ጀምሮ እያንዳንዱ የሥርዓቱ ደንቦች የተቃኙት ወታደራዊ የበላይነትን ለማስገኘት እንደሆነ አስገንዝበውናል። በገዳ ሥርዓት መሪ ሆኖ የሚመረጠው ሰው ከእድሜ አቻዎቹ ብዙ ሰው የገደለው ነው። ከመመረጡ በፊት ሰውን አድኖ ገድሎ ለመረጃነት ይዞ ያልተገኘ ኦሮሞ በገዳ ሥርዓት አይመረጥም። በገዳ ሥርዓት አንዱ ሉባ ከጓደኞቹ መካከል በልጦ ለመገኘት በተለይ ወንዶችን፣ በእናት ማኅጸን ውስጥ ያለ ሕጻንን ጨምሮ ገድሎ ቸብቸቦውን ይዞ መቅረብ የሥርዓቱ አንድ አካል ነው። ባጭሩ የገዳ ስርዓት የገዳዮች ስርዓት ነው።

የገዳ ሥርዓት ምንም ዓይነት የዲሞክራሲ መልክ እንዳልነበረው የሚያሳየው ሌላው አቋሙ የፖለቲካ ስርዓቱ መሪ (አባ ቦኩ) በቤተሰብ ተወራራሽ ወይም ከልጅ ልጅ የሚያልፍ መሆኑ ነው። እውነተኛው ኦሮሞ ምንም እንኳን በቁጥር ትንሽ[ከአስር እንድ] ቢሆንም ወታደራዊ የበላይነትን እንዲያገኝ ያደረገው ይህ ለጦርነት የሰላው አደረጃጀቱ ግን ቁጥሩ እንዲበዛ አድርጎታል። አባ ቦኩ (የፖለቲካ ቢሮው) ከልጅ ልጅ የሚተላለፍ በመሆኑ ተቋማዊ ትውፊቱን (institutional memory) ሲያስቀጥል የወታደራዊ ክንፉ የሚሞላው በጉልበትም፣ በእድሜም የመግደል ችሎታቸው ከፍተኛ በሆኑ መሪዎች ነበር። ይህ በሌሎች የኢትዮጵያ ማኅበረሰቦች ከነበረው ከቤተሰብ ወደ ቤተሰብ ከሚተላለፈው የስልጣን ሽግግር ሙሉ በሙሉ የተለየ ነበር።

ሞጋሳ የገዳ ሥርዓት ምሰሶ ነው። የሞጋሳ ሥርዓት የተጀመረው እውነተኛ ኦሮሞ የሆኑት የቦረናና ባሬንቱ ነገዶች ወረራ ሲጀምሩ የሚወሩት ግዛት እያሰፋ በመሄዱ ቁጥራቸው ሳስቶ ለጥቃት ተጋላጭ እንዳይሆኑ ነበር። በዚህ ጊዜ የወረሩትን አካባቢ ሙሉ በሙሉ ከመግደል የማረኩትን ባሪያ፣ ገባርና ገርባ ቢያደጉት የበለጠ ጠቀሜታ እንዳለው ተረድተው የመጀመሪያ ልምዳቸውን ሻሽለውታል። በዚህ ጊዜ ነበር የጉዲፈቻና ሞጋሳ ሥርዓቶች በስራ ላይ መዋል የጀመሩት። ቦረናና ባሬንቱ ሲስፋፉ በጦርነት የያዙትን ሕዝብ ገድለው ከመጨረስ ይልቅ ባሕሉንና ቋንቋውን በማጥፋት፣ በምንም ዓይነት ማንነቱን ወደ ኋላ እንዳያስታውስ አድርገው የአባቱን ስም ሳይቀር በመቀየር ለጦርነቱ የሚማገድ ኃይል ለማድረግ ነበር ሞጋሳ የተጀመረው። እንዲህም ከተደረገ በኋላ በሞጋሳ የተያዘው ኦሮሞ አልተደረገም ገርባ እንጂ። ገርባ አገልጋይ ብቻ ሳይሆን ኦሮሞው በፈለገ ጊዜ የሚሸጠው ባሪያም ነበር። ለዚህ ምንጭ የኦሮሞ ብሔርተኛው ፕሮፈሰር መሐመድ ሐሰን ከሰላሳ ዓመታት በፊት “The Oromo of Ethiopia: A History, 1570-1860” በሚል ባሳተመው መጽሐፍ ገጽ 126 ላይ የጻፈውን ያነቧል።

የሞጋሳ ስሪት ከልጅ ልጅ የሚተላለፍ ሥርዓት ነበር። በገዳ ሥርዓት መሰረት ገርባ የተደረገው ሕዝብ ማንነቱን እንዲያጣ ተደርጎ፤ ከማኅበራዊ ቦታውም ወጥቶ መሬትም ሆነ ሌላ ንብረት እንዳያፈራ ይከለክላል። ገርባ የኦሮሞ ንብረት ብቻ ነበር። ባጭሩ ገርባ ምንም እንኳን ኦሮምኛ እንዲናገር ቢገደድም ኦሮሞ ግን ፈጽሞ አልነበረም፤ እንዲሆንም የገዳ ሥርዓትም አይፈቅድለትም።

ከ17ኛው እስከ 20ኛው መቶ ክፍለ ድረስ አብዛኛው የባሪያ አቅራቢዎች ሞቲ[የኦሮሞ ንጉሥ] የሆኑት አንጋፋዎች እንደነበሩ የተመዘገበ ታሪክ ነው። በዚህም የተነሳ አብዛኛው ባሪያ ኦሮምኛ ተናጋሪ ነበር። ይህ ማለት ግን ሞቲዎች ለሽያጭ የሚያቀርቡት ኦሮሞዎችን ነበር ማለት አይደለም። በሞቲዎችና አባገዳዎች ለሽያጭ የሚቀርቡት አገልጋይ የነበሩ ገርባዎች ነበሩ። በደቡቡ፣ በምዕራቡና በመካከለኛው የኢትዮጵያ ክፍል ከአባገዳ መር የዘር ጀኖሳይድ የተረፉት ነገዶች እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ በሞቲ ባሪያ ፈንጋዮች ጥቃትን ያስተናግዱ ነበር። ለዚህ የሚከተሉትን እውነታዎች መጥቀስ ይቻላል።

ዳግማዊ አባ ጅፋርን በ1904 ዓ.ም. በሚኖሩበት ጅማ ሄዶ የጎበኛቸው ፊታውራሪ ተክለ ሐዋርያት ተክለ ማርያም አባ ጅፋር «ከአንድ ሚሊዮን በላይ የአካባቢውን ሕዝብ በተለይም የሞችን በባርነት ሽጦ እንደጨረሰው» ኦቶባዮግራፊ [የሕይወቴ ታሪክ] በሚል ባዘጋጁት የታሪክ መጽሐፍ ውስጥ አስፍረዋል።

Achamyeleh Tamiru, [16.10.20 03:10]
በ1916 ዓ.ም. ኢትዮጵያ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት [League of Nations] አባል ለመሆን ባመለከተችበት ወቅት በእንግሊዝ መንግሥት ከፍተኛ ተቃውሞ ቀርቦባት ነበር። የኢትዮጵያን መንግሥት የአባልነት ማመልከቻ ለተባበሩት መንግሥታት ድርጅት [League of Nations] ለማስገባት ወደ ጀኔቫ የተላከው ቡድን መሪ የነበሩት ራስ ናደው አባ ወሎ በፈረስ ስማቸው «አባ መብረቅ» እንግሊዝ ኢትዮጵያ የመንግሥታቱ ማኅበር አባል እንዳትሆን የተቃወመችበትን ምክንያት ለንግሥተ ነገሥታት ዘውዲቱ በላኩት የቴሌግራም መልዕክት፤

«እንግሊዝ ዓለም አቀፍ የመገናኛ ብዙሐን የዘገቡትንና በሱዳን፣ በኬንያ፣ በኤደንና በግብጽ ባሉት የቅኝ ግዛት መንግሥቱ በኩል የሰበሰበውን ማስረጃ በማያያዝ በደቡብ ኢትዮጵያ እየተካሄደ ስለነበረው የባርያ ንግድ ሁኔታ፤ በተለይም የጂማው አባ ጅፋር በከፋ፣ በማጂ፣ በጊሚራና በጉራፈርዳ ሕዝብ ላይ እየካሄዱት ያለው መጠነ ሰፊ የባሪያ ንግድ ለማኅበሩ የፖለቲካ ኮሚሲዮንና ለጠቅላላ ጉባኤ በማቅረብ አባል እንዳንሆን ከፍተኛ ተቃውሞ አቅርቦብናል»

ሲሉ አስረድተዋል።

ሆኖም ግን ኢትዮጵያ ውስጥ በአባ ጅፋር አማካኝነት የሚካሄደው የባርያ ንግድ ባጭር ጊዜ ውስጥ ጨርሶ እንዲታገድና የሰው ልጅ መብት በመላው የአገሪቱ ግዛት እንዲከበር የአልጋወራሽ ተፈሪ መንግሥት ለመንግሥታቱ ማኅበር ቃል በመግባት ኢትዮጵያ ያቀረበችው የአባልነት ጥያቄ ተቀባይነት አግኝቶ ከመስከረም 17 ቀን 1916 ዓ.ም. ጀምሮ ኢትዮጵያ የመንግስታቱ ማህበር 57ኛ አባል ሆና መመዝገቧ በይፋ ታወጀላት።

ባጭሩ በአባ ገዳ የተመራው የኦሮሞ ገዢ መደብ ወረራ ተሳክቶለት ኢትዮጵያን ሙሉ በሙሉ ቢቆጣጠር ኖሮ ሁሉም ባሕልና ቋንቋ ተጨፍልቆና ተሰልቅጦ ዛሬ ሁሉም አንድ ወጥ ኦሮሞ ብቻ ይሆን ነበር። ለዚህ ማሳያው ቀላል ነው። ኦሮሞ በወረራ የያዛቸው የጥንት ነገዶች ሙሉ በሙሉ ወደ ኦሮሞነት ተቀይረዋል። ኦሮሚያ በሚባለው ክልል ውስጥ ከኦሮሞ ወረራ በፊት ይኖሩ የነበሩት ጥንታዊ ነገዶች ሁሉ ጸድተው ማንነታቸውን እንዲቀይሩ ተገድደዋል። ይህም የሆነው በዋናነት በገዳ ሥርዓ ነው። እንደ መልካም ነገር የአዲስ አበባ ልጆች እንዲማሩት እየተፈለገ ያለው ይህንን ጥንታዊ የኢትዮጵያ ነገዶች የጸዱበትን ሥርዓት ነው።

ገራሚው ነገር ዛሬ ገዳን ለሌላው ሊያስተምሩ የተነሱት ባለጊዜዎች «ተበደልን፣ የዘር ጥቃት ደረሰብን» ብለው ሊያለቃቅሱ የነበሩና በጦረኛ አባገዳዎች ተሸንፈው የተያዙ ገርባ ልጆች መሆናቸው ነው። እነዚህ ገርባዎች ዳግማዊ ዐፄ ምኒልክ ተነስተው አባ ላፋዎች [የኦሮሞ የመሬት ከበርቴዎች]፣ ሞቲዎች፣ መልከኞች [የአካባቢ ገዢዎች]፣ አባ ገዳዎች ወዘተ ጠቅልለው ከያዙት መሬት ውስጥ ቀንሰው የሚያርሱት መሬትና የግል ንብረት ባለቤት እስኪያደርጓቸው ድረስ መሬትም ንብረትም እንዳልነበራቸው አያውቁም። ይህን ባለማወቃቸው ዛሬ በኦነጋውያን በየአካባቢው የሚደርሰውን ጥቃትና ተዳፍኖ የቆየው ከሀያ ስምንት በላይ የኢትዮጵያ ነገዶች በሞጋሳ የጠፉበት የገዳ ሥርዓት የወለደውን ጦረኝነት ክፍል ሁለት ለማስቀጠም ገዳን ሊያስተምሩ ይዳዳቸዋል።


ኢትዮጵያ የተወረረችበትን፣ ነባር ነገዶቿ ከርስታቸው የፈለሱበትን፣ 400 ዓመታት ሙሉ በደም ጎርፍ የታጠብንበትን፣ ከ28 በላይ የኢትዮጵያ የጥንት ነገዶች ለወሬ ነጋሪ ሳይተርፍ የጠፉበትን የገዳን ሥርዓት ከጥፋቱ ለተረፉት ማስተማር ስድስት ሚልዮን አይሁዶችን ለጥፋት የዳረገውን የናዚ ሥርዓት ለእብራውያን ልጆች ከማስተማር ተለይቶ አይታይም። የናዚዎቹን ስኬት ለማስተማር የሚፈልጉ የሉም ማለት አይደለም። በደንብ አሉ። ሆኖም ግን ታሪክ በትክክል በመነገሩ ጨካኝ የናዚ ሥርዓት በዓለም ላይ እየተወገዘ እንዲኖርና ተመልሶ እንዳይመጣ ተደርጓል። በአገራችን ግን ታሪካችንን በደምብ ባለማወቃችን፣ የዘር ማጥፋትን የተካሄደበትና ከሀያ ስምንት በላይ የኢትዮጵያ ነገዶች የጠፉበትን ገዳን እንደበረከት እንድንማረው እየተደረግን እንገኛለን። ታሪካችንን ጠንቅቀን ያወቅን ቢሆን ኖሮ የጠፋንበትን ወታደራዊና የወረራ ሥርዓታቸውን እንድንማር ሳይሆን በወረራ በያዙት ባድማ ላይ የነባሩን ሕዝብ ቋንቋ፣ ባሕልና ሃይማኖት አጥፍተው የሰፈሩት የሥርዓቱ ባለቤቶች የሆኑት አባገዳዎች ቋንቋና ባሕላቸውን ላጠፉባቸው፣ መሬታቸውን ነጥቀው ገርባ ላደረጓቸው፣ ባሪያ አደርገው ለሸጧቸው ከሀያ ስምንት በላይ የኢትዮጵያ ነገዶች በይፋ ይቅርታ እንዲጠይቁ ማድረግ እንችል ነበር። 

 


 

 

Read more
no image

 ገዳና እሬቻ

( በአቻምየለህ ታምሩ ) -
 
ዐቢይ አሕመድና የዘረጋው የአፓርታይድ አገዛዝ ባላደራዎች ባለፉት ሁለት ዓመታት ውስጥ ጥንታዊቱን በራራን፤ ዘመናዊቱን አዲስ አበባን አፍርሰው በኦነጋውያን የደነዘዘ አእምሮ ውስጥ በተፈጠረችው ፊንፊኔ ለመተካት ያላፈረሱት የቆየ አሻራና የከተማይቱን ጥንታዊነት የሚመሰክር ምልክት የለም። የከተማ አስተዳደሩን የፖሊስ ሠራዊት ኦሮሚያ ከሚባለው ክልል በመለመሏቸው ለከተማው ከባሕር የወጣ አሳ በሆኑ የፖሊስ ዩኒፎርም የለበሱ ቄሮዎች ተክተውታል። ደብረ ዘይት በሚገኘው ሆራ ሐይቅ ከመስቀል በኋላ ይከበር የነበረውን እሬቻን "ሸገርን ለማስዋብ" በሚል ዐቢይ አሕመድ ግለሰቦችን [አብዛኛዎቹ አማሮች ናቸው] አምስት አምስት ሚሊዮን ብር እንዲያወጡ አድርጎ ባስቋረው ሰው ሰራሽ ሐይቅ ላይ አዲስ አበባ ውስጥ እንዲከበር አዳነች አበቤ በዐቢይ አሕመድ በተሾመች ሳምንት ሳይሞላት አባገዳ ለሚባሉቱ የይዞታ ካርታ ሰጥታለች።
 
ዐቢይ አሕመድ የአዲስ አበባን ይፋዊ ስም ወደ ሸገር ቀይሮ “ሸገርን ማስዋብ” የሚል የማፈናቀያና የጥንቱን የአዲስ አበባ ኗሪ የማጽጃ ፕሮጀክት የቀረጸው የሁላችንም የሆነችን አዲስ ስበባን ለማስዋብ ሳይሆን የኦሮሙማዋን ፊንፊኔ ለመፍጠር ነው። አዲስ አበባ ውስጥ ዐቢይ ባቋረው ሰው ሰራሽ ኩሬ እንዲከበር ቋሚ የይዞታ ካርታ የተሰጠው እሬቻ ዐቢይ አሕመድ "ሸገርን ማስዋብ" የሚል የዳቦ ስም ሰጥቶ እየፈጠራት ላለቸው የኦሮሙማዋ ፊንፊኔ አንድ ማሳያ ነው። ዐቢይ አሕመድም ሆነ ወራሪዎቹ አባገዳዎች አዲስ አበባ ውስጥ ተከብሮ የማያውቀውን እሬቻን አዲስ አበባ ለማክበር ሽርጉድ እያሉ ያሉት የበዓሉ ፍቅር ፈጥርቋቸው ሳይሆን አዲስ አበባ በመውረር የኦሮሞማዋን ፊንፊኔ ለመመስረት በሚያደርጉት እንቅስቃሴ ከ150 ዓመት በፊት እዚህ ነበርን ብለው ለፈጠሩት ተረት እንድ "ማስረጃ" የኦሮሞ ባሕል አድርገው የሚያቀርቡትን እሬቻን አዲስ አበባ ውስጥ እንደነበር አድርገው ማቅረብ የግድ ስለሚያስፈልጋቸው ነው።
 
ከዚህ ውጭ አዲስ አበባ ውስጥ ተከብሮ የማያውቀውን እሬቻን አዲስ አበባ ውስጥ ለማክበር የሚነሱበት አንዳች ምድራዊ ምክንያት የለም። ሆኖም ግን እሬቻም ልክ እንደ ገዳ ሁሉ በታሪክ የኦሮሞ አይደሉም። ኦሮሞ ገዳን የተማረው ከባንቱ ነው። የከባንቱ ሥርዓት የነበረውን ገዳን የወረሰውም ኢትዮጵያን በወረረበት ወቅት ነበር። ስለዚህ የገዳ ሥርዓት የኦሮሞ ሥርዓት ተብሎ በዩኔስኮ ሊመዘገብ ከቶ አይቻለውም። ገዳ እንደ ሥርዓት በዩኔስኮ መመዝገብ ካለበት የኦሮሞ ተብሎ ሳይሆን የባለቤቶቹ የባንቱዎች ተብሎ ነው። ገዳ የኦሮሞ ሥርዓት እንዳልነበር፤ ኦሮሞ ገዳን ኢትዮጵያን በወረረበት ወቅት ከባንቱ እንደተማረው ታሪኩን አጣርቶ የነገረን ከአባ ባሕርይ ቀጥሎ በኦሮሞ ታሪክ ጥናት ቀዳሚ ተጠቃሽ የሆነው ጣሊያናዊው ምሑር ፕሮፈሰር ኢኔርኮ ቸሩሊ ነው።

 ፕሮፈሰር ኢኔሪኮ ቸሩሊ ስለ አካባቢው ታሪክ የተጻፈውን የጥንቱን የዜንጅ መጽሐፍ ዋቢ በማድረግ እ.ኤ.አ. በ1957 ዓ.ም. Somalia: Scritti Vari editi ed Inediti I እና እ.ኤ.አ. በ1959 ዓ.ም. Somalia: Scritti Vari editi ed Inediti II በሚል በጣሊያንኛ ቋንቋ ባሳተማቸው መጽሐፍቱ የመዛገበውን ታሪክ ጠቅሶ ጂን ዶሬስ እ.ኤ.አ. በ1971 ዓ.ም. “ Histoire Sommaire de la Corne Orientale de l'Afrique” በሚል ርዕስ በፈረንሳይኛ ቋንቋ ባሳተመው መጽሐፉ ላይ ታሪኩን እንዲህ ያስቀምጠዋል፤
 
“ዛሬ ሱማሊያ በሚባለው ምድር ሱማሌ ጋላን ተካ። መጀርቲን በሚባለው አካባቢ አንድ መዘክር ወይም የጥንት መጽሐፍ ይገኛል። ይህም ሰነድ ዑባያ በተባለ አካባቢ በሱማሊኛ Galka’yo (ጋል ካ አዮ) የተባለ ቦታ እንዳለ ይጠቅሳል። የቦታው ትርጉም “ጋሎች የለቀቁት [ቦታ] ማለት ነው።. . . ከሰሜን ምስራቅ የመጣው የጋላ ሕዝብ ከመቶ ዓመት በላይ ከዘለቀ ትግል በኋላ ባንቱን ከማዕከላዊ ሶማሊያ አስወጣ፤ [ጋላ] የገዳ ሥርዓትን የወረሰውም ከባንቱ ነው። [በ10ኛው መቶ ክፍለ ዘመን] ሱማሌ ጋላን ወግቶ ከሲማሊያ አስወጣ። ጋላ በገዳ ሥርዓት በመጠቀም በ16ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የኢትዮጵያን ከፍተኛ ለምለም መሬቶች ወረረ” [1]
 
ይህ የቼሩሊ ጥናት በግልጽ እንደሚያሳየው ኦሮሞ የገዳ ሥርዓትን የወረሰው ከባንቱ ሲሆን ሥርዓቱንም ከባንቱ የተዋሰው ኢትዮጵያን ለመውረር ነበር።
 
እሬቻም የኦሮሞ ገዢ መደብ በየስምንት አመቱ ሲያደርግ የኖረውን ወረራ ገና ሳያካሂድ፤ የእርሻ ስራና ሰብል ማምረት ሳይጀምርና ዛሬ ኦሮምያ በሚባለው ምድር ሳይስፋፋ መስከረም በገባ መስቀል በተከበረ በሳምንቱ ሲከበር የኖረው ደብረ ዘይት የአቡዬ የጸበል ሥፍራ በነበረው በሆራ ሐይቅ ነበር። እሬቻ ቃሉ ጭምር የአማርኛ ቃል እንጂ የኦሮምኛ ቃል አይደለም። እሬቻ ኦሮምኛ ነው የሚል ቢኖር የቃሉን የኦሮምኛ ግንድና ቃሉ በኦሮምኛ እንዴት አንደሚረባ ማስረዳት ይጠበቅበታል። የግዕዙ ሊቅ አለቃ ደስታ ተክለ ወልድ "ዐዲስ ያማርኛ መዝገበ ቃላት" በሚል ባሰናዱት መዝገበ ቃላት ውስጥ እንደጻፉት እሬቻ ዋናው ሰብል ደርቆ ከመታጨዱና በአውድማ ተወቅቶ ወደ ጎተራ ከመግባቱ በፊት ቀድሞ የደረሰው ተቆርጦ በበትር በመወቃት ወይም በእጅ ታሽቶ የሚቀመሰው እህል ይሉታል። ለላው ሊቅ ከሣቴ ብርሃን ተሰማም በ1951 ዓ.ም ባሳተሙት "የአማርኛ መዝገበ ቃላት" መጽሐፋቸው የአማርኛ ቃል ስለሆነው እሬቻ የሚነግሩን ትርጉም ተመሳሳይ ነው። በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ ቋንቋዎች ጥናትና ምርምር ማዕከል በ1993 ዓ.ም. ባሳተመው “የኣማርኛ መዝገበ ቃላት” ገጽ 101 ላይ እሬቻ የአማርኛ ቃል መሆኑን በመበየን ተመሳሳይ ትርጉም ይሰጠዋል። ታዋቂው አሜሪካዊ የኢትዮጵያ ታሪክ አጥኚ ቶማስ ኬንም ባዘጋጀው የአማርኛ - እንግሊዝኛ መዝገበ ቃላት ቅጽ አንድ ገጽ 397 ላይ ስለ እሬቻ የአማርኛ ቃልነትና ትርጉም የሚነግረን ተመሳሳይ ነው።
 
በመሆኑም የእሬቻ በዓልን የሚያከበረው አራሹ ገበሬ ክረምቱን በሰላም እንዲያልፍ፤ ያዘመረው እህል ለፍሬ እንዲበቃና እሸት እንዲቀምስ ያስቻለውን ፈጣሪውን ለማክበር ነው። ባጭሩ የእሬቻ በዓል እህል የሚያበቅል አራሽ ገበሬ የሚያከብረው አመታዊ ዝክር ነው።

 የኦሮሞ ብሔርተኞቹ እነ ፕሮፈሰር መሐመድ ሐሰን፣ ዶክተር ነገሶ ጊዳዳ፤ አቶ ቡልቻ ደመቅሳ፤ አቶ ይልማ ደረሳ፤ ፕሮፈሰር ተሰማ ታዓ፤ ወዘተ እንደነገሩን ደግሞ ኦሮሞ ከብት በማርባት የሚተዳደር የነበረ ሲሆን የእርሻ ስራ የጀመረው ዛሬ በሰፈረበት አካባቢ ከረጋ በኋላ ከ17ኛውና ከ18ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ወዲህ ነው። ይህ ማለት የተሰማራበት የስራ መስክ ከብት ማርባት፤ እምነቱ ደግሞ ዋቄ ፈና ነው የተባለው ኦሮሞ የማያበቅለው እህል የሚሽትበትን ወቅት ጠብቆ ሃይማኖቱ አይደለም የተባለውን መስቀልን አሳልፎ መስቀል በሆነ በሳምንቱ እህል እንዲያበቅል፤ እሸት እንዲቀምስ ለሚያስችል ፈጣሪ ምስጋና ሊያቀርብ ይችላል ካልተባለ በስቀር ከብት አርቢ የነበረው ኦሮሞ እሬቻን ማክበር የጀመረው ሸዋን ሲወር ያገኛቸው አራሽና እህል አብቃይ የአማራ ገበሬዎች ያመረቱት ሰብል ለፍሬ እንዲበቃና እሬቻ [እሼት] እንዲቀምሱ ላስቻላቸው ፈጣሪያቸው ያቀርቡት የነበረውን የምስጋና ባሕል በመውረስ ነው። ስለዚህ እሬቻ ከብት አርቢ የነበረው ኦሮሞ ከነ ቃሉ ከሰብል አምራች የአማራ አርሶ አደሮች የወረሰው የምስጋና በዓል ሲሆን ኦሮሞ አካባቢውን ከመውረሩ በፊት ጀምሮ ይከበር የነበረው ደብረ ዘይት በሚገኘው ሆራ ሐይቅ እንጂ አዲስ አበባ ውስጥ አልነበረም።

ከዚህ በተጨማሪ ዛሬ እሬቻ የሚከበርበት የሸዋ ምድር ኦሮሞ አካባቢውን ከውረሩ በፊት በግብርና ሥራ እየተዳደረ ይኖርበት የነበረው አማራ ነበር። ይህን ታሪክ የሚነግረን ኦነጋውያን እንደ መጽሐፍ ቅዱስ የሚጠቅሱት የኦሮሞ ታሪክ ጸሐፊ ጀርመናዊው አይኬ ሐበርላንድ ነው። አይኬ ሐበርላንድ እ.ኤ.አ. በ1963 ዓ.ም. “Galla Süd-Äthiopiens ” በሚል በጀርመንኛ ባሳተመው መጽሐፉ ገጽ 786 ላይ እንዲህ ይላል፤
 
"Im Herzen Äthiopiens, in Regionen, die einst von den Amhara besetzt waren, lebt die Shoah Galla, die oft als Tullema bezeichnet wird."
 
የእንግሊዝኛ ትርጉም፤
 
“In the heart of Ethiopia, in regions once occupied by the Amhara, live the Shoa Galla, often referred to as the Tullema” [2]
 
የአማርኛ ትርጉም፤
 
“በማዕከላዊ ኢትዮጵያ የአማራ ይዞታዎች በነበሩ አውራጃዎች ውስጥ ቱለማ የሚባሉ የሸዋ ኦሮሞዎች ይኖራሉ”
 
እንግዲህ! የኦሮሞ ብሔርተኞች በሙሉ በፈጠሩት ተረት እየተመሩ “ እሬቻን ከ150 ዓመታት በፊት ይከበር ወደነበረበት ወደ ፊንፊኔ መልሰነዋል” የሚሉን በታሪክ የነሱ ወዳልነበረው ቦታና ኦሮሞ አካባቢውን ከመውረሩ በፊት ባላርሥት የነበረው አማራ ያከብረው የነበረውን የሰብል ክብረ በዓል ወርሰው ነው። እሬቻ በእውነት የኦሮሞ ባሕል ቢሆን ኖሮ [ከወያኔና ኦነግ ዘመን በፊት] ክብረ በዓሉን ከሁሉ በፊት መከበር የነበረበት የኦሮሞ አባት የሆነውና ዛሬም ድረስ ከብት በማርባት የሚተዳደረው ቦረን በሚኖርበት ቦረና ውስጥ እንጂ ኦሮሞ ወደ ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ከገባ በኋላ ያገኛቸው የኢትዮጵያ ነገዶች የሚተዳደሩበት የእርሻ ስራ በሚዘወተርበት አካባቢ መሆን አልነበረበትም። በዓሉንም ማክበር የነበረበት የዘላን ኑሮውን በመተው በወረራ ከያዛቸው አካባቢዎች የእርሻ ስራ ተምሮ የኢኮኖሚ ባሕል በመቀየር በተማረው የእርሻ ስራ ኑሮውን በመሰረተው ልጁ ቱለማ ሳይሆን የኢኮኖሚ ባሕሉን ሳይቀይር ዛሬም ድረስ ኑሮውን ከብት በማርባት የሚገፋው አባቱ ቦረን መሆን ነበረበት።

 

 በዚህ ላይ ከቱለማም ኦሮምኛ ተናጋሪ ሁሉ ኦሮሞ አይደለም። ከቦረና ውጭ በየትኛውም የኢትዮጵያ ክፍል ኦሮሞዎቹ ወራሪዎቹ አባገዳዎቹና የነሱ ዘመዶች ብቻ ናቸው። የተቀረው ኦሮምኛ እንዲናገር የተደረገው ተገዶ እንጂ ኦሮሞ አይደለም። ኦሮምኛ የሚናገረው ሁሉ ኦሮምኛ እንዳልሆነ እውነተኞቹ ኦሮሞዎቹ ራሳቸው ምስክር ናቸው። በእውነተኞቹ ኦሮሞዎች ትውፊት ውስጥ «Salgan Borana, sagaltamman gabra» የሚል አባባል አለ። ይህ ወደ አማርኛ ሲተረጎም «ዘጠኙ ኦሮሞ ነው፤ ዘጠናው ገርበ ነው» ማለት ነው። ገርባ ኦሮሞ ሲስፋፋ ያስገበራቸውንና ባርያ ያደረጋቸውን ነገዶች የሚጠራበት ስያሜ ነው። በኦሮሞ በራሱ ትውፊት መሰረት ዛሬ ኦሮምያ በሚባለው ክልል ውስጥ ከሚኖረው ኦሮምኛ ተናጋሪው ሕዝበ መካከል ትክክለኛው ኦሮሞ ከአስሩ አንዱ ብቻ ነው ማለት ነው። ከአስሩ ዘጠኙ ገርበ ወይም በአባገዳዎች በወረራ የተያዘና በኃይል ኦሮሞ የተደረገ ሕዝብ ነው። ባጭሩ እሬቻ የኦሮሞ ባሕል ቢሆን ኖሮ ከሁሉ በፊት መከበር የነበረበት “Salgan Borana” የተባሉት በሚኖሩበት አካባቢ እንጂ “sagaltamman gabra” በብዛት በሚኖሩበት አካባቢ መሆን አልነበረበትም። እንዴውም እሬቻ ከዘመነ ወያኔና ኦነግ በፊት “Salgan Borana” በተባሉት እውነተኞቹ ኦሮሞዎች ዘንድ አይታወቅም።
 
ባጭሩ እሬቻ ኦሮሞ በወረራ ከያዘው ከገርባ የተዋሰው እንጂ አባቱ ከሆነው ከቦረና የወረሰው አይደለም። ከመስቀል በኋላ በእርሻ የሚተዳደር ማኅበረሰብ ያከብረው ከነበረው የምስጋና ቀን ከሆነው ከእሬቻን ሥነ ሥርዓት ውስጥ የኦሮሞ የሆነው የኦሮሞ የገዢ መደብ እሬቻን ከሌሎች ወርሶ የራሱ ሲያደርግ ከቃልቻና ባዕድ አምልኮ ጋር የቀላቀለው ነገር ብቻ ነው። ለዚህም ነው ዛሬ እሬቻ ሲከበር ዛፍ ወትተና ቅቤ እየተቀባ፤ መስዕዋት እየቀረበ [በዳግማዊ ምኒልክ ዘመን እሬቻን ሲያከብሩ ሰው በማረድ መስዕዋት ያቀርቡ እንደነበር በዘመኑ የተመዘገበ የታሪክ ማስረጃ አግኝቻለሁ] ዋቃ ከሚሉት ቃልቻ ጋር ቀላቅለው እያከበሩት የሚገኙት። ይህም በመሆኑ ነው ኦሮሞ እሬቻን ሲወርስ ወደ ባእድ አምልኮና ሃይማኖት በመቀየሩ የተነሳ ጸጋዬ ገብረ መድኅን ሳይቀር እሬቻን ሃይማኖታዊ ሥርዓት አድርጎ ሊያቀርበው የቻለው።
_____
የግርሜ ማስታወሻ፤
 
[1] ትርጉም፡ ግርማ በሻህ in [አምሃ ዳኘው (2012)፥ ሐገራዊ ብሔርተኝነት እና ዘውጋዊ ብሔርተኛነት በኢትዮጵያ፥ ገጽ 118]
[2] ዝኒ ከማሁ፥ ገጽ 171.

 

 

 

 

 

 

 

 

 



Read more
June 29, 2017
ይድረስ፦ መስመራችሁን ስታችሁ እዋዠቃችሁ ለምትገኙ አማሮች

(Gizenew Demelash)

1. ግንቦት ሰቦት በሚባል ፀረ አማራ ድርጅት ውስጥ የተሰገሰጋችሁ ጥቅመኛ የአማራ ተወላጆች

2. "የአማራ ህልውና ለኢትዮጵያ አንድነት" በሚል የኦነግን፣ ህውሃት እና መሰሎቻቸው አማራን የመክሰሻ ድርጅት መሰረትን ለምትሉን አማሮች

3. በሀገረ ቤት ሆናችሁ በምርጫ ቦርድ አበል በመሿሿም እና መሻሻር ላይ ብቻ ለተወሰናችሁ እና አማራነትን እንደ መውረድ ቆጥራችሁ ለምትመፃደቁ የትግል እንቅፋቶች

4. ዛሬም የዋለልኝን ፈለግ በመከተል ከፀረ አማራ ድርጅቶች አጀንዳ በመቀበል አማራን በጎጤ ማህበራት ለመከፋፈል እየሰራችሁ ለምትገኙ ጭንጋፎች

5. ኢሳት በተባለው የፀረ አማራ ሀይሎች ሚዲያ ውስጥ ተሰግስጋችሁ እንደ ይሁዳ አማራነትን ስታሻሽጡ ለምትውሉ የአማራ ተወላጆች

6. ለዚህ ትውልድ በይፋ የተገለጣችሁ የዘመናችን ዋለልኞች፦ አቶ ሀብታሙ አያሌው፣ አቶ አቻምየለህ ታምሩ፣ አቶ ደመቀ ገሰሰ የኔዓየሁ፣ አቶ ሙሉነህ ዮሀንስ (አስናቀው አበበ/ህዝብ ያሸንፋል) ... ለአብነት

“ኦሮሚያን” አገር የማድረጉ ሂደት አዲስ አበባን ለኦሮሞች በማስረከብ ዛሬ ተጠናቋል። “አዲስ አበባ ኬኔ” ብሎ የተሰለፈና ፀንቶ የታገለው የኦሮሞ ብሔርተኛ እንደ ሁሌው ዛሬም ከጠየቀው በላይ አፈሰ። የአማራ ኢሊት ነን የሚሉ የተማሩ ደንቆሮዎች “የኢትዮጵያ እንጂ የአማራ ብሔርተኝነት የሚባል ነገር የለም” እያሉ አፋቸውን ሲያሰፉ ከወሬ ይልቅ የፖለቲካ ስራ ላይ የተጉት ትውልዳቸውን በብሔርተኝነት የቀረፁና ያደራጁ የኦሮሞ ኢሊቶች በድል ላይ ድል እያስመዘገቡ ከባዶ ተነስተው የአገር ባለቤት ለመሆን በቁ። እኛ ደግሞ የኛ የሆነውን ሁሉ እያጣን አለን።


የዛሬ 25 ዓመት እነ ወልቃይትን፣ እነ ጠገዴንና ጠለምትን፣ እነ ራያና ቆቦንን፣ እነ መተከልን ፣ ከፊል ሸዋን ለሌሎች አሳልፎ የሰጠ የአማራ ሕዝብ ጠላት የሆነው ብአዴን ዛሬ ደግሞ የአማራ ሕዝብ ባልመከረበት ሁናቴ አዲስ አበባን ለኦሮሞቹ ፈርሞ በማስረከብ የአባቶቻችንን ዕርስት አስነጠቀን። ብአዴን የህውሃት ክንፍ መሆኑን አጥቸው አይደለም። በስማችን እየነገደ ያለ ቡድን ከመሆኑም በተጨማሪ ቢያንስ በማከዕከላኛውና ከታች ባለው አባላት ዘንዳ አማራዎች አሉ በሚል ነው። መችም አሳዛኝም አሳፋሪም ታሪካዊ ክስተት ነው። እውነቱን ለመናገር ወደ 50+ ዓመታት ለሚጠጉ ግዜዎች የሚቆረቆርለት እና ዛሬን ሊመክት የሚችል ድርጅት ማቋቋም የተሳነው ኢሊት ያፈራ ሕዝብ በአለም ላይ ከአማራ ውጪ ሌላ ሕዝብ የሚኖር አይመስለኝም።

ይሄ ሀቅ እኔን ሁሌም የሚያሸማቅቀኝ ጉዳይ ሆኖ አለ። አማራ እንደ ሕዝብ ዛሬ ባለበት ሁናቴም ቢሆን ህልውናው ያለሁ በወለዳቸው ጭንጋፍ ልጆቹ ሳይሆን በአዛውንቶች ፆምና ፀሎት ብቻ ነው። ይሄ እውነታም አጥንቴ ድረስ ዘልቆ የሚሰማን እውነታ ነው።"መሬት ሲያረጅ ሙጃ ያበቅላል" ይባላል። በራሳቸው፣ በዘራቸውና በብሔራቸው የሚሸማቀቁ፣ ጣታቸውን ወደታላላቆቹ ከመቀሰር ባለፈ "የኔ" የሚሉትና የሚሞትቱለት ግብ የሌላቸው፣ በቆልማማ ብዕራቸው አይናቸውን ጨፍነው ዙሪያቸውን ከመጨርገድ ባለፈ ይሄ ነው የሚባል ትልም ለመተለም የማይችሉ ፣ የነሱ መደንዘዝ ሳያንስ የወንድሞችን እቅድ ለማክሸፍ ሌት ተቀን የሚተጉ ፣ እንደ ሰው ራዕይ የሌላቸው "ሙጃ" ግለሰቦች በዙብንና የሕዝባችንን ጣር አረዘሙት።

ለማንኛውም መጪው ግዜ ከዛሬው እጅግ የከፋ ነውና አማራ ከታረደባቸው እንደ ጅማ ካሉ አካባቢዎች ሸሽተህ አዲስ አበባና ዙሪያዋ የከተምክ አማራ ወገብህን አጥብቀህ እሰር። ሞርተኛ ለመሆን አይደለም። ፈርቿ እያስፈራራሁም እንዳይመስላችሁ። አማራን በብሔርተኝነት የማሰባሰቡ ትግል አማራ ነን ብለው ሰይፍ የመዘዙበትን ውራጅ አማራዎች ለመሻገርና የአማራን ሕዝብ ከጥፋት ለመታደግ ከገመትነው በላይ ግዜ እንደሚዎስድብን ስለተገነዘብኩ ነው። የነቃው እና የአማራን ሕዝብ በብሔሩ እያሰባሰበና እያደራጀ ያለው የአማራ ኢሊት በስንት ድካም ያሰባሰበውን ሕዝብ ለመበተን ሌት ተቀን እየጫጫረ ያለውን ሌላኛውን አማራን ለማሸነፍ የሚደረገውን ትግል እጅግ አድካሚና አሰልቺ መሆኑን ቀርቤ አይቻለሁ።

ለማንኛውም #ቤተአማራ ለአማራ ብቸኛ መድህን ናትና ጠበቅ እናድርጋት።
Read more
June 28, 2017
አዲስ አበባ ፤ የሸዋ አማራዋ መዲና - “”የአባቶችን ርስት አልሰጥም!!!!!”

አዲስ አበባ፤ ሸዋ የአማራዋ መዲና ናት ስንል....

ኢህአዴግ በአሁኑ ውሳኔው የኦሮምያን ልዩ ጥቅም በአዲስ አበባ ለማስከበር አረቀቅኩት ያለው አዋጅ ፤ በእርግጥም እንደሚፀድቅ ተማምኖ ማቅረቡ ፤ ያልበሰለ እና ታሪካዊ የአማራን ድርሻ እና ባለቤትነት ያገለለ አሰተሳሰብ በመሆኑ ሊታረም ፣ ሊታይ እና ሌሎችም በሄሮች እና ብሄረሰቦች እንዲሁም ፣ የሽዋ አማራው በአዲስ አበባ ምክር ቤት ወንበር የመወሰን መብቱ ሊጠበቅለት ይገባል። አዲስ አበባ አማራው ራሱን ሰውቶ ያነገሳት ከተማ ናት። ለአማራው ልዩ ጥቅምም በአዲስ አበባ ከምክር ቤት ወንበር ጀምሮ እስከ ሰሜን ሽዋ የአማራ ክልል ዞን ልዩ ተጠቃሚነት የታሪክ ባለቤትነቱ ሊገለል አይገባም።


"የአማራ" መንግስት ስርዓት ውስጥ "የሸዋ አማሮች" አዲስ አበባን መርጠው ፣ ቆርቁረው ፣ አደራጅተው እና አሳድገው ለሀገር እና ለአለም ዲፕሎማሲያዊ መቀመጫነት አብቀተዋታል የ"ብሄረተኞነት"ከተማ ሳይሆን የሁሉም ብሄርች ከተማ መናገሻ አድርገዋትል። ይህ አፈታሪክ አይደለም ማንበብ ለሚችል ሰው Sorenson, Imagining Ethiopia , (New Brunswick, NJ Rutgers University Press) p.12 ወይም Messay, p.36 ፣ እና Ibid., p.23 እንዲሁም Taddesse,1972,pp 132 -135; Bahiru, p.75; Donald, C.pp.21 -22 ያገላበጠ አንባቢ ሁሉ አያጣውም። ብዙሃኑ "የሸዋ አማራ" ያቆማት እና ዙፋኑን ያፀናባትን ከተማ የአንድ ብሄር ተጠቃሚነትን ብቻ ባረጋገጠ ሁኔታ ከፖለቲካዊ ቁማርነት እየገፉ ፣ የአንድ በሄር እንብርት ናት። ሲሉ ማውራት ለኔ ትንሹ ልጅ ሲያለቅስ ትልቁን አንተ ዝም በል ብሎ የትልቁን ንብረት ቀምቶ እንደመስጠት ነው ምቆጥረው ። 



አዋጁ ፍትሃዊ ማይሆነው እኩል ተጠቃሚነትን ሳይሆን የአንድ ቡድን ውቅታዊ ጥያቄ ለመመለስ ያለመ መሆኑ ላይ ማተኮሩ ነው። በእርግጥም የመንን ፣ ቀይ ባህርን ፣ ኤርትራን እና ጅቡቲን አንድም በአቅም እጥረት አልያም በፖለቲካ ድክመት እያሳለፍን ታሪካችንን ሽጠን በልተነዋል። ከታሪካዊ ባለቤትነት ይልቅ የፖለቲካ ጥቅም የሚያሸንፈው መንግስት በተፈጠረበት ጊዜ ሁሉ ብዙ ነገር ከእጃችን ወድቋል። ሀገርን መገንባት ሳይሆን ብሄርን በመገንባት በተጠመደ ስርዓት ውስጥ ደግሞ አንድን በር መዝጋት ብዙ ሽህ በሮችን እንደመክፈት ይቆጠራል ይታያልም። አዲስ አበባን መስርተው ፣ ጠቅመው ፣ የመንግስት አመራር መዋቅር ሹመው፣ አብዛኛውን የኢኮኖሚ ምንጮች አፍልቀው፣ የአዲስ አበባን የግዛት ክፍሎች ይገዙ የነበሩ፣ የአዲስ አበባ መስራች ና ፈጣሪዎች ለኢኮኖሚ እንቅስቃሴያቸው አዲስ አበባን ማዕከል አድርገው የመሰረቱ ነበሩ። የአማራ ህዝብ የሸዋ መኳንንቶች ምስጋና ይግባቸው እና የሁሉም ብሄሮች መኖሪያ አድርገዋታል።


በቅርቡ በተካሄደ ጥናትም የብሄር ማንነት የሌለው ሰፊ ህዝብ የሚኖርበት ክልል አዲስ አበባ ነው። ከ63 በመቶ በላይ የሚሆነው አማራ በሆነባት ከተማ መሬቱን የአንድ ብሄር ሃብት አድርጎ ማውጅ ምን አይነት ብስለት የጎደለው አሰራር መሆኑን ያሳያል።


ብዙሃኑ የሸዋ አማራ በድህነት እየኖረ ስልጣን አልባና እንደ አንድ ቡድን በየስርዓቱ እየተመዘበረ ባድማው ውስጥ ራሱን መፈለግ ወጋችን ፣ ታሪካችንም ነው። ይህ አዲስ አበባ ባለዎለታዋን የምትዘነጋ ከተማ አይደለችም ለእምየ ሚኒልክ ሃውልቷን ፊቱን ኦዞራ ያቆመችው በምሃል ጊዩርጊስ ወደ መንበሯ "የሸዋ አማራ ሀገር" ነው። ታዲያ እንዴት ነው በኦሮሞ የተከበበችው አዲስ አበባ ፊንፊኔ ብቻ ምትሆነው። ቋንቋዋን ምትቀይረው። የሌላው ብሄር ልጆችስ በአባታቸው ባድማ ወዴት ይወድቃሉ???


የማይመለሱ ብዙ ሽህ ጥያቄዎች ቢኖሩም ያባቶቻችንን ርስት አንሰጥም ብያለሁ እና አማራ አዲስ አበባን የሚያውቃት ማንም ከሚያውቃት በፊት ነው። Pankhurst Rassam አገላለጽ ጎንደር በ19ኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ አጋማሽ ከሰሜን፣ ከምእራብና ከደቡብ ለሚነሱ የሲራራ ነጋዴዎች ሁነኛ ማረፊያ ማዕከል ነነበረች በዚያ ዘመን ከጎንደር ወደ ማህል አገር የሲራራ ነጋዴዎች መተላለፊያ በርካታ አቅጣጫዎችና ቅርንጫፎች ነበሩት። በዚህም አንዷ አዲስ አበባ እንደነበረች በመፅሓፋቸው ከትበውታል።


ከጎንደር ሰፈራቸው የተነሱ ነጋዴዎች በጣና ሃይቅ በኩል አድርገው ወደ ይፋግ ከተሻገሩ በሁዋላ በሁለት በመከፈል አንዱ ወገን ወደምስራቅ አቅጣጫ ወደ ሸዋ (አዲስ አበባ) ሲያቀና ሌላኛው ወገን ደግሞ ወደደቡብ ወደ ጎጃም ያመራል። ወደ ደቡብ አቅጣጫ የሚዘልቀው የንግድ መስመር፣ ባሶ፣ ጉድሩ፣ በማቋረጥ ወደ ጎንደር መጥተው በጨውና ከውጭ አገር በሚገቡ እቃዎች የሚለወጡ "ወርቅ፣ የዝሆን ጥርስ፣ የከርከሮ ቀንድ፣ የግስላ/ ነብር ቆዳ፣ የጉማሬ ቆዳና ጋሻ እንዲሁም የባሮች" ምንጭ ወደሆኑት ከፋና ጃንጀሮ ይደርሳል ። ከእነዚህ በተጨማሪ ነጋዴዎች በሸዋ (አዲስ አበባ)፣ በሐረርና በዘይላ በኩል በማለፍ ወደ ሶማሌ የበርበራ ወደብ፣ "የዝሆን ጥርስ፣ ባሮችና ፈረሶች" ይዘው በመሄድ በልዋጩ ብረት፣ ጥጥና የህንድ ሸቀጦችን ለአገር ውስጥ ገበያ ያቀርቡ ነበር ።


አገር አቋራጭ ንግድ ወይም የሲራራ ንግድ በአማራ ክልል ለነበሩት በርካታ ገበያዎችና የንግድ ማእከላት መፈጠር ዋንኛ ሚና ተጫውቷል። በ18ኛውና በ19ኛው ምእተ አመታት የጎንደር ፣ የጎጃም እና የሽዋ ነጋዴዎች ምቹ መደላድል የፈጠሩባት እና ጠምደው ያረሱበት ርስታቸው ናት።


ለመሬት ባለቤትነት ታሪክ ተያይዞ የሚጠራው የንግድ መስመር ሲሆን በ19ነኛው ምእተአመት መጀመሪያ ላይ ከፍ ያለ ኢኮኖሚያዊ ጥቅም ከነበራቸው የንግድ መስመሮች የሸዋው የንግድ መስመር ነው። አጼ ሚኒልክ የመንግስታቸውን መቀመጫ ከተማ ከአንኮበር ወደ እንጦጦ ከማዘዋወራቸው በፊት አንኮበር፣ አንጎለላና አልዩ አምባ የታወቁ የገበያ ማእከላት በመሆን አገልግለዋል። በተለይ አንጎለላ ወደ ሰሜን፣ ምስራቅ፣ ምእራብና ደቡብ የሚጓዙ የአማራ፣ የኦሮሞ፣ የሶማሌ፣ የጉራጌ፣ የሐረሬና የደንከሌ ነጋዴዎችን ቀልብ የሚስብ የንግድ ማእከል ነበር።
ከሸዋ የንግድ መስመር ወደሰሜን አቅጣጫ በአድዋና በአንጣሎ አድርጎ የጎንደርና የሸዋ ሲራራ ነጋዴዎች መገናኛ ወደነበረው ምጽዋ የሚደርስ ነበር።


የጎጃም ነጋዴዎችም ወደ ሰሜን የሚያልፍ ሌላ የንግድ መስመርም ነበራቸው። ከዳንግላ ባሪያ፣ ከዘጌ ቡና ጭነው ወደ ጎንደር የሚነግዱ ነጋዴዎች በቡሬ፣ በዳንግላ ወይም ዘጌ በይስማላና በደልጊ አድርገው ወደ ጎንደር ይደርሳሉ። ከወሎና ከምስራቅ ጎጃም የሚነሱ ነጋዴዎች ደግሞ በደጀንና በብቸና በኩል አድርገው እንጦጦ ይሰፍራሉ። በሞጣ፣ አዴት፣ ወረታ አድርገው የሚጓዙት ወደ አገራቸው ወደ ደሪጣ የሚገቡት ነጋዴዎች ጭነታቸውን ደሪጣ ካላራገፉ በእንፍራዝና በምንዝሮ በኩል ተሻረው ጎንደር ይገባሉ። ወደ ታጁራ ወደብ የሚነግዱ የወሎና የአማራ ሳይንት ነጋዴዎች ደግሞ በብቸና፣ ቃሉ፣ ወረሂመኑና ደሴ አድርገው ይጓዛሉ። ንጉስ ተክለ ሃይማኖት በ1878 ዓም በእንባቦ ጦርነት በአጼ ምኒሊክ ድል እስከሆኑበት ድረስ ባሶ የደራ የንግድ ማእከል በመሆን አገልግሏል። የጎጃም የሽዋ እና የጎንደር ነጋዴዎች ማረፊያ ከነበሩት የሽዋ አማራ መስመርም አዲስ አበባ ቀደሚ ናት።


የንግድ መስመሮችና ማዕከሎች እድገት በ20ኛው ምዕተ ዓመት እና የአዲስ አበባን ታሪካዊ የአማራ ባለቤትነት ከምንጩ እንመርምረው።


የሽዋ አማራ መናገሻዋ አዲስ አበባ በአማራዎች መቆርቆር የንጉሰ ነገስቱ መኖሪያ ብቻ ሳይሆን የአገሪቱ ማዕከላዊ የንግድ ማእከልና ገበያም መጀመሪያ ከነበረበት ወደ አዲስቱ ማዕከል እንዲዛወር ዋና ምክያት ሆኗል። የአዲስ አበባ ገበያም ሸቀጦች ግብይት በብዛትና በአይነት የደራበት፣ የውጭ አገር ሰዎች እንደ አገሬዎቹ ነጋዴዎች በሰፊው የሚነግዱበት ነበር። እነዚህ የውጭ አገር ነጋዴዎች ከአዲስ አበባ ውጭ ባሉ ከተሞችም የንግድ ስራቸውን በወኪሎቻቸው አማካይነት ያከናውኑ ነበር። አዲስ አበባ ማእከላዊ ገበያ መሆኗ ከደቡባዊው የአገሪቱ ክፍሎች በአማራ ክልል ታዋቂ ወደነበሩት አሮጌዎቹ ገበያዎች የሚመጣው የገበያ ሸቀጥ እንዲቀንስ አድርጓል። በተለይ ደግሞ አዲስ አበባ የፓለቲካና የኢኮኖሚ ማእከል መሆኑዋን ተከትሎ የተሰራው የአዲስ አበባ-ጅቡቲ የባቡር ሐዲድ 75 በመቶ ያክሉ ወደአገሪቱ የሚገባና ከአገሪቱ የሚወጣ ሸቀጥ መተላለፊያ በመሆኑ ፣ የጎጃም የንግድ መስመር ከሰሜንና ሰሜን ምእራብ ወደ አዲስ አበባ መተላለፊያ መሆኑ እንዲቀር ቀጥተኛ ተጽእኖ አድርጓል። በአንድ በኩል በመተማ በኩል ወደ ውጭ ከሚላኩ ምርቶች በስተቀር ከውጭ አገር ወደ ጎጃምና ጎንደር ገበያዎች የሚገቡ ልዩ ልዩ ሸቀጦች መጠን ቀንሷል።


ዳሩ ግን ወርቅ፣ የዝሆን ጥርስ፣ ዝባድ እና ቡና የመሳሰሉ ሸቀጦች ተፈላጊነታቸው በማደጉ ምክንያት የሆሮ፣ አሶሳ፣ ጊዳ፣ ቤንሻንጉል፣ ወንበራና የሌሎች የደቡብ ምእራብ አካባቢዎች ነጋዴዎች ቡሬ እየተገናኙ ሸቀጦቻቸውን በአሞሌ መለዋወጣቸው አልተቋረጠም ነበር። ስለዚህም ቡሬ በአዲስ አበባ፣ መተማና ምጽዋ ገበያዎች ከፍተኛ ተፈላጊነት ያላቸው የቆዳ፣ ሌጦ፣ ሰም፣ ቅቤ፣ በርበሬ ምርቶች መገበያያ ዋና ማእከል ነበረች። ከ1920ዎቹ በኋላ አስመራ ከበስተደቡብ በኩል ለሚመጡ ነጋዴዎች አንዳንድ ሁኔታዎችን በማመቻቸቷ፣ በእነዚህ አገልግሎቶችና በርካሽ ዋጋ በሚገዙ ጥራት ያላቸው ሸቀጦች የተማረኩ የጎጃምና የጎንደር ነጋዴዎች እስከ ኢጣሊያ ወረራ ድረስ ወደ አስመራ እየተጓዙ ይነግዱ ነበር።


በሃያኛው ክፍለ ዘመን የንግድ መስመሮች ብቻ ሳይሆኑ ወደ ውጭ በሚላኩና ወደአገር ውስጥ በሚገቡ ሸቀጦች አይነትም ላይ ለውጥ ታይቷል። በከፍተኛ መጠን ለውጭ ገበያ ተፈላጊነት የነበራቸውን የዝባድ፣ የዝሆን ጥርስና የወርቅ ምርቶች ቡና ሲተካቸው ወደ አገር ውስጥ ከሚገቡ ሸቀጦች ሁሉ ከፍተኛ ገበያ የነበረው ደግሞ አቡጀዲ ነበር። ሸቀጦችን ወደ ውጭ ገበያ በማውጣትና ከውጭ ወደ አገር ውስጥ በማስገባት ረገድ ከፍተኛ ሚና የነበራቸው የሲራራ ነጋዴዎችም ቀስ በቀስ የፈረንሳይ፣ የህንድ፣ የግሪክና የአርመን ተወላጅ በሆኑ ነጋዴዎች ተተኩ።


ከ1933 ዓም በኋላ ባለው ዘመን የነበረው ንግድ በአገር ውስጥ የተመረቱ የእርሻና የኢንዱስትሪ ውጤቶችን መግዛትና መሸጥን ያካትታል። እስከዚህ ዘመን ድረስ የነበረው የውጭና የአገር ውስጥ ንግድ ግን በአገር ውስጥ በተመረቱ ምርቶች ላይ ብቻ የተመሰረተ ነበር። የአዲስ አበባና ሌሎች ከተሞች መቆርቆር፣ የአዲስ አበባ ጅቡቲ የባቡር ሐዲድ ግንባታ በ1907 መጠናቀቅ እና በኢጣሊያ ወረራ ዘመን የመኪና መንገዶች መሰራት ለኢንዱስትሪ ማደግ ቁልፍ ሚና የተጫዎቹ ጉዳዮች መሆናቸው ይታመናል። በሌላ አገላለጽም በኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ውስጥ የኢንዱ]ስትው ዘርፍ ሚና መጫዎት የጀመረው ከነጻነት በሁዋላ ከነበረው ዘመን አንስቶ ነው። ስለዚህም በአማራ ክልል ስለኢንዱስትሪ መስፋፋት ይዞታ የምናደርገው ውይይት ኢጣሊያ ከኢትዮጵያ ከተባረረበት ዘመን ጀምሮ ይሆን ዘንድ ተገቢ ቢሆንም የንጉሰ ነገስቱና የደርግ አገዛዞች እጅግ የተማከለ የአስተዳደር ስርዓት ስለነበራቸው የኢንዱስትሪው ዘርፍ በክልሉ ንግድ ውስጥ የነበረውን ሚና የሚያሳዩ መረጃዎችን ማግኘት አልተቻለም። እነዚህ ሁለት አገዛዞች አንድ ወጥ ፖሊሲዎች መከተላቸው የንግድና የኢንዱስትሪ ስራዎች እንዳያድጉና እንዳይስፋፉ ዋንኛ ምክንያት ሆኗል።


እስከ ኢጣሊያ ወረራ ድረስ በኢትዮጵያ የነበረው የንግድ ትስስርና ልውውጥ በአማራ ህዝብ ይሁንታ የመገበያያ ገንዘብ ታትሞ በስራ ላይ በመዋሉ፣ የንግድ ፈቃድ ምስክር ወረቀት እና የዋስትና ስርዓት በመዘርጋቱ ምክንያት ወደላቀ ደረጃ ተሸጋገረ .። በኢጣሊያና በኢትዮጵያ መንግስት መንገዶች በመሰራታቸውም ነጋዴዎች ከአንዱ የኢትዮጵያ ክፍል ወደ ሌላው ተንቀሳቅሰው ለመግዛትና ለመሸጥ የተሻለ ሁኔታ ተፈጠረላቸው።


የውጭ ንግድን በተመለከተ ቀደም ባለው ዘመን ከፍተኛ ድርሻ የነበራቸው ዝባድ፣ ወርቅ፣ የዝሆን ጥርስ፣ ቅቤ፣ የቀንድ ከብቶችና ጥጥ የመሳሰሉት ሸቀጦች በቡና፣ ቆዳና ሌጦ፣ ጥራጥሬና የቅባት እህሎች ተተኩ። ቡና ለበርካታ አመታት አገሪቱ ወደ ውጭ ከምትልካቸው ምርቶች 50% እስከ 65% የሚሆነውን ሸፍኖ በመቆየቱ ምክንያት የአማራ ክልል ለአለም አቀፍ ገበያው የነበረው አስተዋጽኦ ሊያቆለቁል ችሏል። ይህም ሆኖ ግን ክልሉ ቆዳና ሌጦና እንዲሁም ጥራጥሬና የቅባት እህሎችን በማምረት ለውጭ ገበያ ሲያቀርብ ቆይቷል። ዳሩ ግን እነዚህ ምርቶች በአገሪቱ የውጭ ንግድ ውስጥ የተወሰነ ድርሻ ያላቸው በመሆኑ የውጭ ንግድ በጠቅላላው የአማራ ክልል አርሶ አደርን የገቢ ምንጭ በማሳደግ ረገድ የተጫወተው ሚና አነስተኛ ነው። እንዲያውም የእለት ፍጆታ ከፍተኛ የሆነውን ጤፍ ፣ ማር እና ቅቤ በማቅረብ የአዲስ አበባን ውበት መልሷል።


ወደአገር ውስጥ በሚገቡ ምርቶች ንግድ ረገድም ቀደም ሲል በርከት ያለ ድርሻ የነበረው ጨርቃጨርቅ መካከለኛና ከፍተኛ ዋጋ በሚያወጡ ሸቀጦች ተተክቷል። ይህም ሊሆን የቻለበት ምክንያት ወደ አገር ውስጥ በሚገቡ ሸቀጦች ዋጋ መናርና ወደውጭ በሚላኩ ጥሬ እቃዎች ዋጋ መውደቅ ሊከሰት በሚችለው የተዛባ የንግድ ሚዛን የሚደርሰውን የኢኮኖሚ ጉዳት ለመቀነስ መንግስት በተከተለው ከውጭ የሚገቡ ሸቀጦችን በአገር ምርት የመተካት ፖሊሲ አማካይነት ነው። የዚህ ፖሊሲ ውጤት፣ የጨርቃጨርቅ ውጤቶችን መጠጦችን፣ ለስላሳ መጠጦችንና ስኳርን የመሳሰሉ አላቂ የፍጆታ እቃዎችን የሚያመርቱ ኢንዱስትሪዎች ከመጠን በላይ እንዲበረክቱ አድርጓል። እነዚህ ›=ንዱስትሪዎችም በአዲስ አበባ ዙሪያ፣ የባቡር ሃዲድ በሚያቋርጣቸውና ሰፋፊ ገበያ ባለባቸው አካባቢዎች ብቻ ተከማችተው የሚገኙ ነበሩ። የአማራ ክልል ገበያዎች ደግሞ በመሰረተ ልማት አለመኖርና በየገቢ መጠን ዝቅተኛነት ምክንያት የእነዚህን ከውጭ የሚገቡ ሸቀጦችን ለመተካት የተቋቋሙ ኢንዱስትሪዎች ቀልብና ትኩረት የሚስብ ስላልነበረ ክልሉ በንጉሱ ዘመን በነበረው የተዛባ የኢንዱስትሪዎች ስርጭት ተጎጅ ሆኖ ኖሯል።


በተወሰኑ የምርት ዘርፎች ላይ የተሰማሩት እነዚህ ኢንዱስትሪዎችም በአብዛኛው በውጭ አገር ሰዎች ይዞታ ስር የነበሩ ናቸው። በኢንዱስትሪው ዘርፍ የውጭ ካፒታል በርካታውን መጠን መሸፈኑ መንግስት ከሚከተለው ለዘብተኛ ፖሊሲ የመነጨ ነበር። የውጭ ባለ ሃብቶችን ለመሳብ የንጉሰ ነገስቱ መንግስት ብር 200,000 እና ከዚያ በላይ የመነሻ ካፒታል የሚያስመዘግቡ የውጭ አገር ባለሃብቶችን ከትርፍ ከሚገኝ ገቢ ሊከፈል ከሚገባው ቀረጥ ነጻ የሚያደርግ ፖሊሲ ነበረው። ፖሊሲው በአንጻሩ ከፍተኛውን የንግድ ገቢ ቀረጥ መጠን ከተጣራ ትርፍ ላይ 15 በመቶ እንዲሆን፣ ትራክተሮችና ኬሚካሎች ቀረጥ ሳይከፈልባቸው እንዲገቡ ሲፈቅድ በአገር ውስጥ የሚመረቱ ሸቀጦችን በሚያስገቡ ላይ ደግሞ ከፍተኛ የቀረጥ ምጣኔ የሚጥል ነበር ።


አዲስ አበባ አማራው ራሱን ሰውቶ ያነገሳት ከተማ ናት። ለአማራው ልዩ ጥቅምም በአዲስ አበባ ከምክር ቤት ወንበር ጀምሮ እስከ ሰሜን ሽዋ የአማራ ክልል ዞን ልዩ ተጠቃሚነት የታሪክ ባለቤትነቱ ሊገለል አይገባም።
Read more
የአማራ ምሁራን ከወደቁበት የአንድነት አዚም እንዲላቀቁ ፓለቲካዊ ፈውስ ያስፈልጋቸዋል!

ኃያል ሰው
ሰኔ 21 ቀን 2009 ዓ.ም
ከአዲሲቷ የአማራ ምድር
ፈለገ ጊዮን
ባህር ዳር


የ1960ዎቹ የአማራ ትውልድ በሰሩት ታሪካዊ ስህተት ዛሬ የአማራ ህዝብ ለሚገኝበት ዘርፈ ብዙ ችግር ዋና ምክንያት ሆኖ ይገኛል። ዘውዳዊውን ስርዓት በጭፍንና በቂ ዝግጅት ባልተደረገበት ሁኔታ እንዲወገድ የአማራ ልጆች እንደ ዋለልኝ ያሉትያሉት የተጫወቱት ሚና በአማራነት ላይ የተከፈተው የመጀመሪያው ታሪካዊ ጠላትነት ነበር። የዘውዳዊው ስርዓት በአማራ ልጆች አጃቢነት መወገድ ለአማራ ጠላቶች ሰፊ በርን ከፈተላቸው። ሶማሌ በምስራቅ፣ ሻቢያና ወያኔ በሰሜን፣ ሱዳን በምዕራብ በአገራችን ላይ ፀረ አማራና ኢትዮጵያዊ ትግል አቀጣጠሉ። የዚያ ትውልድ ታሪካዊ ስህተት በተለይም የአማራ ምሁራን ማንቀላፋት ለፀረ አማራና ፀረ ኢትዮጵያ እንቅስቃሴ መፈጠር ጉልህ ሚና ነበረው። በቀይና ነጭ ሽብር ሰበብ አገር ወዳድ የአማራ ልጆች እየታደኑ ተረሸኑ፣ ከአገር ተሰደዱ፣ ወደ እስር ተወረወሩ። በአማራ ማንቀላፋትና አለመንቃት በኢትዮጵያ ትቅደም ካባ ስር "አማራ ይውደም" የሚል የትግል ስልት ውስጥ ለውስጥ ተቀጣጠለ። ሻቢያና ወያኔ የደርግን ቡትቶ ለብሰው በገጠርና በከተማ አማራን የማፈንና የመግደል ዘመቻ አፋፋሙ።


እነዚያ ለኢትዮጵያ ብሎም ለአፍሪካ አንድነትና ነፃነት የተሟገቱ ብርቅዬ ንጉስ በሆያ ሆዬ ጩኸት ወደ መቃብር ተሸኙ። የአፄ ኃይለ ስላሴ በግፍ ከስልጣን መውረድና የ60 ሚኒስትሮች በአደባባይ መረሸን የአማራ ውድቀት የማንቂያ ደወል ነበር። ሆኖም ግን አማራ ከመንቃት ይልቅ በየዋህነት እራሱን በማጥቃት ከፀረ አማራ ኃይሎች ጋር ተሰለፈ። ህወኃት በ1967 ዓ• ም ሲፈጠር ዋናው ዓላማ አማራን ማጥፋትና ኢትዮጵያን ማፈራረስ ነበር። ወያኔም በበኩሉ ከሻቢያ በተሰጠው ተልኮ መሰረት የፀረ አማራና ፀረ ኢትዮጵያ ትግሉን ለ17 ዓመታት አቀጣጠለው። ያኔም በተመሳሳይ የአማራ ልጆች ከአማራ ጠላቶች ጋር በማበር አብረው ታግለውና መንገድ መርተው ወያኔን ለዙፋን አበቁት።

ወያኔ ግን አማራ ላደረገለት ቸርነት ከሻቢያና ከኦነግ ጋር በማበር አማራውን በበደኖ፣ ጉራ ፈርዳ፣ አርባጉጉና ሌሎችም አካባቢዎች በእጀ ዙር አሳረደ። ሻቢያ፣ ወያኔና ኦነግ በፀረ አማራና ፀረ ኢትዮጵያ አባዜ ተለክፈው በአማራው ላይ የፈፀሙት ግፍ ታሪክ ይቅር የማይለውና አሳፋሪው የጥላቻ ገድል ነው። አማራው ባለፉት ዘመናት ለአገሩና ለወገኑ ቆስሏል፣ ደምቷል፣ ህይወቱን ሁሉ መስዋዕት አድርጓል። ለዚህ ታላቅና አገር ወዳድ ህዝብ የተበረከተለት ስጦታ ግን ስደት፣ መፈናቀል፣ እስርና ሞት ነው።

ፕሮፌሰር አስራት ወልደየስ የነገሮች ሁኔታ ስላላማራቸው አማራው ተሰባስቦ ለህልውናው የሚታገልበትን ድርጅት መዐሕድን መሰረቱ። የመዐሕድ መፈጠር ያስደነገጠው ወያኔም እኒህን ታላቅና ብርቅዬ ምሁር በማስወገድ መዐሕድን አፈራረሰው። ዛሬ በአማራው ላይ እየደረሰ ያለው የተጠናና የተደራጅ ዘር የማጥፋት እንቅስቃሴ እረፍት በነሳቸው የአማራ ልጆች መመከት ሲጀምር በአማራ ልጆች በሚፈጠሩት የአማራ ድርጅቶች ላይ የጥላቻ ሰይፍ ከውስጥም ከውጭም መመዘዝ ተጀመረ። 


ሞረሽ ወገኔ የለኮሰው እሳት፣ ቤተ አማራ ያቀጣጠለው የአማራ ብሔርተኝነት መንፈስ ምድሪቷን ሲያጥለቀልቅና አህብንም ከአዴኃን ጋር ከመዋሃዱ በፊት ባደረገው ሰፊ የማንቃት ስራ አማራን ከተኛበት ሲቀሰቅስና በኋላም ዳግማዊ መዐሕድ ተመስርቶ አማራነት በሰማይና በምድር ሲዘመር፣ የአማራ ተጋድሎ ሲቀጣጠል፣ ጠላቶቻችን የሚይዙትና የሚጨብጡት ሲጠፋ፣ የአማራ ምሁራን ግን እንደ ኤማሆስ መንገደኞች የአንድነትና የኢትዮጵያዊነት ሙሾ ያንጎራጉራሉ። 

በተለይ የፕሮፌሰር አስራት አማራነትን የመታደግ ህልም የነበረው ዳግማዊ መዐሕድ እንደገና በምጥ ሲወለድ ፀረ አማራነት ጫጫታው ጨመረ። የጥላቻ ጦሮች ከእየ አቅጣጫው መወርወር ጀመሩ። ሄኖክ የሺጥላ፣ ሙሉቀን ተስፋው፣ መንበሩ አያሌው፣ መለክ ሃራና ሌሎችም የአማራ ከዋክብቶች በብዕራቸው ለአማራ ዘብ ቆሙ፣ ደረታቸውን ለጥላቻ ጦር ሰጥተው አማራ ተነስ እያሉ የአማራን ትንሳኤ በምድሪቷ ላይ አስተጋቡ።

በዚህ ሁሉ ውስጥ ለኢትዮጵያ አንድነትና ነፃነት ቆሜያለው የሚለው አርበኞች ግንቦት ሰባት የአማራን መደራጀትና ወደ ትግል መግባት በግልፅና በስውር ማጥላላት ጀመረ። የጀግኖችን ተጋድሎ የወያኔ ቡትቶ እያለበሰ አቅጣጫ ለማስቀየር ተውተረተረ። በ2008 ዓ• ም በኦሮሞና በአማራ ህዝቦች አማካኝነት ፀረ ወያኔ ትግል ተቀጣጠለ። የአማራ ተጋድሎ የተባለውን የአማራ ህዝብ መስዋዕትነት አርበኞች ግንቦት ሰባት ለራሱ ርካሽ የፓለቲካ ትርፍ ለመሰብሰብና የአማራን ህዝብ የማንነትና የህልውና ተጋድሎ አቅጣጫ ለማስቀየር ተሯሯጠ። የአማራ ህዝብ በደምና በአጥንቱ ባቆያት አገር ውስጥ ሆኖ፣ አማራን አግልሎ፣ አማራን አፍኖ፣ ስለ አንድነትና ኢትዮጵያዊነት መስበክ "የሞኝ ለቅሶ መልሶ መላልሶ" ዓይነት ነው ዛሬ ለአዲሱ የአማራ ትውልድ። አማራውን ከእርስቱ ያገለለ፣ አማራውን ከመብቱ ያጎደለ፣ አማራውን ከአጠቃላዩ አገራዊ ፓለቲካና የለውጥ ጉዞ ያራቀ ትግል የትም አይደርስም። የአገሬ ሰው ሲተርት "በማን ላይ ቆመሽ እግዜርን ታሚያለሽ" ይላል።


በመሆኑም ለዚች አገር ህልውና፣ ነፃነትና ኩራት የአንበሳውን ድርሻ ያበረከተውን የአማራን ህዝብ መብትና ማንነት ማክበር ለድርድር የሚቀርብ አጀንዳ አይደለም። የአማራ ህዝብ በሻቢያ፣ በወያኔና በኦነግ ተሸውዷል፣ ዳግም በግንቦት ሰባት ግን አይሸወድም። አብረን ታግለን ነፃ እንውጣ፣ አገራችንን ከጥፋት እንታደግ ከተባለ በመጀመሪያ የአማራን ህዝብ ማክበር፣ ድርጅቶቹን ማክበርና በእውነትና በፍቅር መኖርን ይጠይቃል። የአማራ ህዝብ ጠላቶች የፍትህ ጠላቶች ናቸው፣ የነፃነት ጠላቶች ናቸው፣ የታሪክ ጠላቶች ናቸው፣ የእውነት ጠላቶች ናቸው። አሁን ወደ ፊት ለመጓዝና ከፊታችን ያሉትን መሰናክሎች በድል ለመወጣት አጠቃላዩ ፓለቲካችንና የአማራ ምሁራን የተንሸዋረረ እይታ ፓለቲካዊ ፈውስ ያስፈልገዋል። ከውሸትና ከተራ የድብብቆሽ ጨዋታ ነፃ መውጣት ያስፈልጋል።

የአማራ ህዝብ ማንነቱ ህልውናውና የከፈለው አኩሪ ገድል እስካልተበረለት ድረስ ትናንትናም፣ ዛሬም ሆነ ወደ ፊት ለአንድነትና ለኢትዮጵያዊነት መንፈስ መጠናከር የሚዘመረው መዝሙር "ውዳሴ ከንቱ" ነው። የአማራ ምሁራን ድንዛዜ፣ የዘመናት እንቅልፍ፣ የአዙሪት ጉዞ፣ ትውልዱን የማስበላት ጅላጅል የአንድነት ጨዎታ ይብቃ። ከዚህ በኋላ አማራነትን ዘምሩ፣ አማራነትን ስበኩ፣ አማራነትን ከፍ አድርጉ፣ ለአማራነት ተጠሉ፣ ለአማራነት ተወገዙ፣ ለአማራነት ተሰደዱ፣ ለአማራነት ተነቀፉ፣ ለአማራነት ታገሉ፣ ለአማራነት ሙቱ። ይህ ሲሆን የእናንተ ህሌና ተፈወሷል ማለት ነው፣ ጤናማ ሁኗል ማለት ነው፣ ትክክለኛ ነገር ማሰብ ጀምሯል ማለት ነው።

አማራነት ዳግም ለድርድር አይቀርብም!!
አማራነት በአዲሱ የአማራ ትውልድ ከፍ ብሎ ይዘመራል!!
ድል ለገናናው የአማራ ህዝብ!!
ውድቀት ለዘመናት የአማራ ጠላቶች!!
Read more
አማራ ወዳጆችን ማብዛት፤ ባላንጣዎችንም መቀነስ የሚችለው በራሱ ጠንክሮ ሲወጣ ብቻ ነው!

(መርከቡ ዘለቀ) 

በወቅቱ ባለው ተጨባጭ ሁኔታ በአማራ ህዝብ ላይ እጣታቸውን የሚቀስሩ ቡድኖች ብዙ መሆናቸውን እየተመለከትን ነው። በእርግጥ ህወሓትና ግብረ አበሮቹ የሀገር ሀብት እስከ ዳር ደንበሯ እየዘረፉ ባለበት ዘመን ለሀገር ጠበቃ ሆኖ የተገኘ ሁሉ ጠላት ሊበዛበት የግድ ነው፤ የሚጠበቅም ነው። ከአማራ ህዝብ ታሪካዊ ጠላቶች (ህወሓት፤ ሻብዕያና ኦነግ) በተጨማሪ የዛሬዎቹ ግንቦት 7 እና ሀገራዊ ንቅናቂ ተብየው ቡድንም የአማራን ህዝብ የሚወክሉ ድርጅቶችን በአገኙት አጋጣሚ ሁሉ በማውገዝ ላይ ይገኛሉ።

አሁን ግን እጅግ እየገረመንና እየመረረን የመጣው ግንቦት 7 የተባለው ሳያፈራ የጨነገፈው የምውታን ስብስብ የሚፈጥረው የማያባራ ንትርክ ነው። ለዚህም ዋናው ምክንያት የግንቦት7 ከአሳዳሪዎቹ የተሰጠውን የቤት ስራ ለመስራት ሲል ነው በአማራ ስም የተደራጁ ቡድኖችን በባላንጣነት የፈረጀው።

ስለእውነት ግን ግንቦት 7 ለምን በአማራ ስም የተደራጁ ቡድኖችን ያወግዛል? ለምን ጸረ-ኢትዮጵያና በኢትዮጵያ አንድነት ላይ የጠራ አቋም ከሌላቸው ቡድኖች ጋር አብሮ ለመስራት እየታተረ በኢትዮጵያ አንድነት ላይ የማይደፈርስ አቋም ካላቸው የአማራ ድርጅች ጋር መስማማት/አብሮ መስራት ተሳነው?

እኔ ግንቦት 7ን ባለፈው አንድ አመት ውስጥ ከሚያስተላልፋቸው ፕሮፓጋንዳዎች አንፃር ስመለከተው ራሱን በራሱ እያጠፋ/እየገደለ (ስዊሳይድ እየፈጸመ) ያለ ድርጅት መሆኑን ነው። ይህ እሳቤ እውነት የሚሆነው ግን ግንበት 7ን እንደ ሀገራዊ ድርጅት አድርገን ከወሰድነው ነው። አሁን አሁን ግን ግንቦት 7 አገራዊ ድርጅት መሆኑ ቀርቶ ዘረኛና ጸረ-ኢትዮጵያ ድርጅት መሆኑን እያስመሰከረ ነው። ዘረኛነቱን ባወጣው የድርጅቱ ውስጠ ድንብ (ከአማረኛ በተጨማሪ ሌላ ቋንቋ ማወቅ አስፈላጊ መሆኑን የገለጸበት) በሚገባ ተገለጾ ይገኛል፤ ጸረ-ኢትዮጵያነቱም የሻዕቢያ ተላላኪ በመሆኑና ከሌሎች ጸረ-ኢትዮጵያ ቡድኖች ጋር በጋራ ኢትዮጵያን ለማፍረስ በሚያደርገው አንቅስቃሴ ይገለጣል።

ግንቦት 7 የህወሓትን መንግስት ማስወገድ(በህልሙ) የሚፈልገው ስልጣን ከህወሓት ወደ ግንቦት 7 ሰዎች በማሸጋገር ሌላ ዘረኛና የጥፋት ሰርአት ለመመሥረት እንጅ ሥር ነቀል ለውጥ በኢትዮጵያ በማምጣት ሁሉም ዜጎች እኩል የሚስተናገዱባት ሀገር ለመፍጠር አይደለም። ለዚህም ነው የህወሓትን በቋንቋ ላይ የተዋቀር ፌደራሊዝም እንዲቀጥል የሚፈልገው፤ ለዚህ ነው በዘር ላይ የተዋቀሩ ቡድኖችን ሲቀላቀሉ የህወሓትን ዘራኛ እና አግላይ አስተዳደር የሚቃወሙ ቡድኖችን የሚኮንነው።

ግንቦት 7 በቋንቋ ላይ የተመሠረተውን የወያኔ ክልላዊ አስተዳደር እንዳለ እቀበላለሁ ከሚልባቸው ምክንያቶች አንዱ የግብረ አበሮቹን ፍላጎት ለማሟላት ሲሆን የእነርሱም ምኞት በህወሓት ዘርኛ መንግስት ከአማራ ህዝብ የነጠቁትን ሰፊ መሬት እንደያዙ በሂደት ለመሸሽ ነው። ነገር ግን በእውነት የግንቦት 7 ጥረቅሞች የፖለቲካ ሰዎች ናቸው ወይ? አስተማማኝ አጋሩን አውግዞ ከመሰናክሉ ጋር የሚዶልቱ፤ በአሜሪካ ውብ ሆቴሎች እየተንፈላሰሱ አረበኞች ነን እያሉ በአረበኛ ስም የሚቀልዱ፤ ስለ ኢትዮጵያ እንታገላለን እያሉ ከኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች ዘንድ የሚሸጎጥ/የሚወተፉ፤ ጦር ሜዳ ሳይውሉ ነውጡን የፈጠርነው እኛ ነን እያሉ ያለ ሀፍረት በአደባባይ የሚዋሹ፤ ውጤት በሚስገኝ ስራ ላይ ከማተኮር ይልቅ በየጊዜው የንትርክ መድረክ ያሚዘጋጁ፤ ስለ ኢትዮጵያ እንታገላለን እያሉ በጀግና ኢትዮጵያውያን ደም እና አጥንት ተለወሶ የተጻፈውን የኢትዮጵያ ታሪክ ኢሳት በተባለው ሚዲያቸው የሚያርክሱ ከሆነ ግንቦት 7 ጤና የጎደላቸው ሰዎች ስብስብ እንጅ ሌላ ሊሆን አይችልም። ምክንያቱም ግንቦት 7 የጤነኛ ሰዎች ስብስብ ቢሆን ኑሮ ጸረ-ኢትዮጵያ አቋሙን ለማራመድ እንኳ አካሄዱን ከአጋሮቹ ከወያኔ እና ከሻዕብያ ይማር ነበር። በአርግጥ ከኦነግ ሊማር አይችልም ምክንያቱም ኦነግም ኢትዮጵያ ውስጥ ገብቶ አንድ ጥይት እንኳ ሳይተኩስ በለንደን ሆቴሎች እየተዝናና ኢትዮጵያን አናፈርሳለን የሚል መናኛ ድርጅት በመሆኑ። ኦነግ መፈክሩ ብቻ ሳይሆ የሚገርመው ህልሙን ለማሳካት የሚጠቀምበት ስልት/ ስተራቴጅም ከንቱ ነው። ስለ እውነት ግን አንድ ጥያቄ አለኝ።

ከዚህ ጸረ-አማራ እና ጸረ-ኢትዮጵያ ከሆነው ግንቦት 7 ድርጅት ጋር አሁንም አባል ሁነው የሚደክሙ የአማራ ተወላጆች ካሉ እነርሱም በእውነት አብደዋል ማለት ነው። እርግጥ ነው ከአንድ አመት በፊት ብዙዎቻችን ተሸውደን ነበር። ስለ ኢሳትና ግንቦት 7 በየቀኑ ወሬ/ዜና ሳንሰማ ከዋልን አንድ ትልቅ ነገር እንዳመለጠን ይሰማን ነበር፤ ስለ ግንቦት 7 ሲወራ የተስፋ ጭላንጭል ይታይን ነበር። የግንቦት 7ን ድብቅ አጀንዳ በብዕራቸው ለተፋለሙና ላጋለጡ ውድ ኢትዮጵያን ምስጋና ይግባቸውና አሁን በግንቦት 7 ላይ የነበረው ተሰፋና መልካም ስሜት በሀገር ውስጥ ሙሉ በሙሉ በሚባል ሁኔታ ላይመለስ ሙቶ ተቀብሯል። የሚቀጥለው ሥራ ግንቦት 7 እንደ ህወሓት ስረ ሰዶ/ገንግኖ ሳያስቸግር በሁሉም መስክ መፋለምና ማጥፋት ነው።

 የአማራን ህዝብ ከጥፋት ለመታደግ ከእውነት እየሰሩ ላሉ ቡድኖች የማስተላልፈው መልክት የአማራ ህዝብ ብዙ ወዳጆች እንዲኖሩትና የባላንጣዎቹም ቁጥር እንዲቀንስ ከተፈለገ ብቸኛው አማራጭ መንገድ አማራ በራሱ ጠንክሮ መውጣት አለበት የሚል ነው። ባለፈው ሩብ ክፍለ ዘመን ማንም እየተነሳ የአማራን ህዝብ ሲያዋርድ፣ ሲዘርፍ፣ ሲያሳድድ፣ በግፍ ሲገድል፣ ደም እና አጥነቱን የገበረበትን ታሪካዊ መሬቱን ሲነጥቀው የኖረበት ብቸኛው ምክንያት አማራ ጠንክሮ ባለመውጣቱ/ባለመደራጀቱ እንደሆነ ሁላችንም የሚያስማማ አብይ ጉዳይ ሆኗል።

ለዚህም ነው ተልካሻው ግንቦት 7 እንኳ ሳይቅር ያለ ምንም ሀፍረትና ፍርሀት ከ30 ሚሊዮን በላይ የሚሆነውን የአማራ ህዝብ እራስህን ከጥፋት ለመከላከል መደራጅት የለብህም እያለ እያፌዘ የሚገኘው። ይህ ትዕቢት ህወሓትና ሻዕቢያ ከሚያሳዩት ትዕቢትም በላይ ነው። ምክንያቱም ሁለቱ የአማራና የኢትዮጵያ ጠላቶች የትዕቢታቸው ምንጨ ለረጅም ጊዜ ማንም ሳይነቃ በወታደራዊ ኃይል መዘጋጀታቸው ብቻ ነው። ግንቦት 7 ግን በአውላላ ሜዳ ላይ የሚጮህ ከንቱ ሲሆን ሌላውን ሊያጠቃ ይቅርና እራሱን ለመከላከል እንኳ የማይችል ቡድን ነው።

ለመሆኑ ግን ግንቦት 7 በየትኛው አቅሙና ህጋዊ ሰውነቱ ነው የሌሎችን የመደራጀት መብት ቻሪና ከልካይ የሆነው? ግንቦት 7 ውስጣዊ ማንነቱ ሻዕቢያና ወያኔ መሆኑ እየታወቀ ከግንቦት 7 ጋር አብሮ ለመስራት የሚመኝ የአማራ ድርጅትስ እንዴት ሊኖር ይችላል? የግንቦት 7ም ሆነ የሀገራዊ ንቅናቄው ኢለማ አማራና ኢትዮጵያ ናቸው ። ለዚህ ነው ግንቦት 7 በሚያካሂደው ስብሰባ ላይ ሁሉ በአማራና በኢትዮጵያ ታሪክ ላይ የሚዘምተው።

ግንቦተ 7 አማራንና ኢትዮጵያን ለማጥቃት ከሚጠቀሙባቸው ስልቶች አንዱ ሰርጸ ደሰታ እንደገለፀው “የወያኔ የክት ሰዎችን” በመጠቀም ነው። ለዚህም ፕሮፌሰር መስፍን ወ/ማሪያምን በሲያትል ስብሰባ ተገኝተው ያደርጉትን የወረደ ንግግር እንደምሳሌ መውስድ እንችላለን። ግን ስለ እውነት እንነጋገረ ከተባለ ፕሮፌሰሩ አሁን ኢትዮጵያ በታሪኳ አይታው የማታውቀው ቀውስ ውስጥ በገባችበት ወቅት ስለ ኢትዮጵያ አንድነት፤ ስለመተሳሰብና በጋራ ስለመስራት ነው መስበክ/መናገር ያለባቸው ወይስ ሊያግባቡ በማይችሉ ጉዳዮች ላይ? አጼ ቴዎድሮስ ያለ ጊዜያቸው የተፈጠሩ ታላቅ መሪ መሆናቸው እየታወቀ አፄ ቴዎድሮስ ከህዝቡ ጋር አልተግባቡም ነበር ማለት ከፕሮፌሰሩ የሚጠበቅ የወቅቱ ንግግር ነው ወይ?

ኢትዮጵያ ከሁሉም ብሄር ብሄረሰብ ከተውጣጡ ጀግና እና አረበኛ ልጆቿ ተከብራ የኖረች ሀገር መሆኗ እየታወቀ ጀግናው በላይ ዘለቀ ጎጃሜ ቢሆንም ማንነቱ ኦሮሞ ነው ማለት በእውነት እንኳስ የፕሮፌሰር ንግግር ሊሆን ቀርቶ ፌደል ያልቆጠረ ሰው እንኳ ሊናገረው ይገባል ወይ? ሰረጸ ደስታ ሰለ ኦረሞ ደጋግሞ እንደገለጸው አሮሞ እኮ የራሱ ጀግና አላጣም ነበር፤ ችግሩ ጀግኖቹን ሁሉ የነፍጠኛ ወዳጆች ናቸው ብሎ በመካዱ ባዶ እጅኑ መቅረቱ ነው ። እንበልና ጀግናው በላይ ዘለቀ ኦሮሞ ነው ብለን ብንቀበላቸው ፕሮፌሰሩ ምን ይፈጠር ነው የሚሉን? አማራ ጀግና የለውም ለማለት ከሆነ ፈጽሞ አያስኬድም።

በእውንት አንድ ስሙን ለጊዜው የማላሰታወሰው ወንድሜ ስለ ፕሮፌሰሩ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ በለጠፈው ጽፍ ለጽሁፉ የሰጠው ርዕስ “መገለባበጥ እንደ—— መክሸፍ እንደ ፕሮፌሰር መስፍን” የሚል ነበረ፤ እውነት ነው በጣም ከሽፈዋል ፕሮፌሰሩ። በነገራችን ላይ ስለ ኮሌኔል መንግስቱ ኃይለማሪያምና የወታደራዊ መንግስት የውድቅት መንስኤዎች በሚያትት መጽሃፍ ላይ እንዳነበብኩት መንግስቱ ኃይለማሪያም እጅግ ካዘነባቸው ምሁራን መካከል ፕሮፌሰር መስፍን ወ/ማሪያምና ዶ/ር ኃይሉ አርአያ ይገኙባቸውል። መንግሰቱ ኃይለማሪያም እንደሚለው ወያኔ 1983 ዓ.ም ሰሜን ሸዋ በደረሰበት ወቅት ምሁራኑ ለኢትዮጵያ አዋጭ መንገዶችን ከማቅረብ ይልቅ ለወያኔ አስተዋፆ በሚያደርጉ ጉዳዮች ላይ ማተኮራቸውን በማንሳት በወቅቱ እንዳዘኑባቸው አንብቢያለው።

ስለዚህ ግንቦት 7 የወያኔን የክፉ ቀን ልጆች ከየቦታው እየመዘዘ ለመጠቀም የሚያደርገው ትርፍ የማያስገኝ አካሄድ ውድቀቱን ከማፋጥን ውጭ ሌላ ትርፍ አያስገኝለትም፣ ስልቱ ተነቅቶበታል፣ የክት ሰዎችም እነማን እንደሆኑ እየታወቀ ነው።

ሌላው ላለፈው 40 ዓመት ሙሉ ኢትዮጵያን ለማፈረስ የሻዕብያና ወያኔ አሽከር ሆኖ ሌት ከቀን ሲሰራ የኖረውና አሁንም ከዚህ ነውረኛ ሰራው ያልታቀበው አቶ ሌንጮ ለታ በሲያትሉ ስበሰባ “የኢተዮጵያ ጉዳይ ያሳስበኛል” ሲል የምጸት ንግግር እንዳደረገ አነበብን። ይገርማል! ስለ አቶ ሌንጮ ለታ ምንነት አቶ ሰርጸ ደስታ በሚያስደት ሁኔታ የገለጸው ስለሆነ መድገም አያስፈልገም። ዶ/ር ብረሀኑ ነጋም የአሻንጉሊቶችን ስብስብ (ሀገራዊ ንቅናቄ ተብየውን) ኢትዮጵያን የሚመጥን ድርጅት ነው በሚል ያደረገውን ንግግር እንዲሁ በድረ ገጽ አነበብን ። በእውነቱ ኢትዮጵያን የሚወክለውና የሚመጥነው ኢትዮጵያን ለማፈረስ ሲጥር የኖረውና አሁንም ኢትዮጵያ ብሎ መጥራት የሚጸፈው፤ የኢትዮጵያን ሰንደቅ ዓለማ ሲያይ የሚበረግገው የሌንጮ ለታ ድርጅትና የሻዕቢያ ተላላኪ የሆነው የግንት 7 ድርጅት በአንድ ላይ የመሠረቱት የጥፋት ቡድን እንዴት ነው ኢትዮጵን የሚመጥነው? ምን አልባትም በውስጥ ወይራ ንግግር ደ/ሩ ማለት የፈለገው ኢትዮጵያን ለማፍረስ አቅም ያለው ጸረ-ኢትዮጵያ ድርጅት መሥረተናል ለማለት ሊሆን ይችላል። ይኸኛውም ሀሳብ ቢሆን ሊሳካላቸው የሚችል አይደለም።

ኢትዮጵያ እጅግ የምትገርም ሀገር ናተ። በክፉ ቀን ከጎኗ ተሰልፈው መሰዋት የሚከፍሉ እንዳሉ ሁሉ ችግር በገጠማት ቁጥር ከቅጥረኞች ጋር በማበር ያለማንም ተከላካይ የቡድን ጥቅማቸውን ለማሳካት የሚሮጡ ብዙ ናቸው።በተለይ በአሁኑ ወቅት ከዘረኛው ህወሓት ትግሬ በተጨማሪ ኦነግና ግብረ አበሮቹ አሁን እየሰሩት ያለው የቆሸሸና ታሪክ ይቅር የማይለው ጥፋት ይህንኑ ነው። ከመላው ኢትዮጵያውያን ጋር በመተባበር የሁሉም ጠላት በሆነው በወያኔ ላይ ክንዳቸውን ማንሳት ሲገባቸው እንገነጠላልን፤ በኢትዮጵያና በኢትዮጵያዊነት እንዲሁም በባንዲራዋ ላይ መደራደር ይገባናል ይሉናል። ሀገረ ውስጥ ያለው የህወሓት ቡችላ ኦህዴድም በአዲስ አበባ ላይ እየሰራ የሚገኘው ሴራ ከኦነግ ጋር በመተባበር ነው። ለመሆኑ ግን ከሃዲውና ዘራፊው ወያኔ ያለማንም ተከላካይ የሚተላልፈው የክህደት ውሳኔ ተቀብሎ የሚኖር ህዝብ ሊኖረ እንደማይችል እንዴት ኦህዴዶች/ኦነጎች መረዳት ተሳናቸው? ኦህዴዶች እና ኦነጎች የሸዋ ኦሮሞ ጀግኖችን እያዋረዱ ለምን በአዲስ አበባ ላይ መስገብገብ አበዙ? የሸዋ ጀግኖችን ከጠሉ ጀግኖቹ ከሌላው ወገናቸው ጋር ተባብረው የመሠረቷትን ከተማ ለምን ይፈልጓታል? ግለሰቡን ከጠሉ ንብረቱን መመኝት አያስኬድም። የኦህዴዶችና ኦነጎች ዘዴ ግልጽ ነው። የገቢያ ግርግር ለሌባ ይመቻል እንደሚባለው የወቅቱን የፖለቲካ ቀውስና የአማራን አለመጠናከር ተጠቅመው አዲስ አበባን በግርግር ለመንጠቅ ነው። የወያኔ ስልትም እንዲሁ ግልጽ ነው። የአማራን የትግል አቅጣጫ ማስቀየርና ጠላቱንም ማብዛት ነው።

ወደ ማጠቃለያ መልክቴ ስመለስ በአማራ ስም ተደራጅታችሁ አማራን ከጨርሶ መጥፋት ለመከላከል እየተንቀሳቀሳችሁ የምትገኙ ቡድኖች ሁሉ መረዳት የሚገባችሁ አብይ ጉዳይ አማራ ከፍተኛ ፈተና ውስጥ የገባ መሆኑን ተርድታችሁ ይህን ከፍተኛ ፈተና በአሸናፊነት ለማለፍ በአንድነትና በጽናት በመቆም ቆራጥ እና ሀገር ወዳድ ወገናችሁን ማደራጀትና ወደ ትግል መምራት ይኖርባችኋል። እያንዳንዱ አማራም በሀወሓት ትግሬና በግበረ አበሮቹ የተገፈፈውን ነፃነቱን ለማስመለስ የትኛውንም አይነት መሰዋትነት ለመክፈል ዝግጁ መሆን ይኖርበታል። ልጆቻችን በኢትዮጵያ እንደዜጋ ተከብረውና መብታቸው ተጠብቆ እንዲኖሩ ከፈለግን እኛ መሰዋት ልንከፍል የግድ ነው። ማለፋችን ላይቀር ስደትንና ውርደትን ልጆቻችን አውርሰን ማለፍ የለብንም።

ድል ለኢትዮጵያ!
Read more
February 28, 2016
no image

My Comment on Bete-Amhara, the Recent Amhara Secessionist Facebook Movement

Some Amhara friends have started a movement to walk away from the Ethiopian Union and to start an independent Amhara Republic. They cited the suffering Amhara people faced since the coming in to power of TPLF as the main reason behind their secessionist movement. The movement believes, as I understood it, secession is the only way for Amhara people to survive. They claim that secession is not an issue of choice of what is best for Amhara rather it is the very means of survival. As expected, they have received opposition from many people and as well some acceptance mainly from Amhara people. Some have labeled it as a racist movement. Despite all the noise, I want to show what is on the ground, what options Amhara as a people have and ways for creating economically benefited Amhara people.
Regarding the union/secession saga, Amhara has three options, in my opinion.

1. Continuing the status-quo: Amhara will continue to be one of the regions of Ethiopia and TPLF through its Amhara Nationalist Democratic Movement (ANDM) wing will continue to administer Amhara. This is what we were being experimented on. The problem with this option is Amhara has been losing in every economic indicator you can possibly imagine. Here are some of the statistics I recall: Amhara is the region of the highest level of poverty in the country, the highest HIV rate in the country, the highest in infant mortality rate, the highest death in relation to child delivery etc. Everyone who loves Amhara/Ethiopia should give it a second thought as to what other options Amhara should experiment on so that it will improve the above mentioned horrifying economic statistics. My personal assessment is the status quo should change.

2. Replace ANDM with Real Amhara Party and Focus on Regional Growth and Development: the advantage with this one is Amhara stays in the Union and might achieve economic growth. This might give the answer to the very question some Amhara friends are raising. But it is not without challenges, the main ones being the difficulty of replacing corrupted ANDM and then the impossibility to work with the national government. Against all the odds, if this can be made happen – it might help many disadvantaged Amhara people reclaim economic advantages that might level them with the rest of the country.

3. Secession: if option number 2 cannot hold – may be – secession is the best we have got. In my understanding – nothing can get worse than the status-quo. However, this is close to an impossible thing. In a country of no independent electoral board – referendum is unthinkable. Or I am not aware of what kind of plan the movement has if referendum is impossible. At the same time – what economic plan the coming secessionist group has; how to deal with border issues (recall Eritrea) and the like should be addressed. Their plan must be appealing too.

What I like about the Movement

In my life time – Amhara people have been acting as the keepers of Ethiopia. Some, even, went too far to claim that there is no a nationality called Amhara – they cite the dictionary meaning of nationality/Ethnic group to convince others that a nationality called Amhara does not exist. Some claim their nationality is Ethiopian not Amhara. This is not a bad thing by itself. A part of me feel proud to be a part of the society that feels union is superior over secession and as well prefer inclusiveness to loneliness. The consequence of such thinking, however, was devastating. No word can tell you about the consequences better than the relative economic statistic (I mentioned above) of Amhara region.

While every other region was trying to help develop their respective region – Amhara were running here and there to tell others that we shouldn’t be ethnically divided. This created a void in the region – Amhara become what we call in Amharic ወልዶ መካን!!! In the past twenty something years – no Amhara elite showed interest to work for Amhara people – because they thought self-love is RACISM. I will talk about the misperceptions related to racism below. In my opinion – the void created by Amhara Unionist thinking (by ignoring ቆሎ ቆርጥሞ ያስተማራቸወን ህዝብ) coupled with the anti-Amhara TPLF agenda – help create Amhara as the poorest region in the world (as reported by Aljazeera).

What I like about Bete-Amhara movement is it fills the void created by Amhara Unionist thinking. It focuses on the economic lives of the poor Amhara and try to come up with what they believe is the best solution. For Bete-Amhara to be a legitimate movement – it shouldn’t have the right solutions to the problems Amhara are suffering. In my opinion – they idea of walking away from a thinking that says – Ethiopia even at the expense of Amhara (the traditional Amhara thinking) – to – who cares for Ethiopia if it doesn’t provide equal opportunity and label playing ground for Amhara – is a great step forward. It might change the game TPLF was playing for quarter a century.

Another Big Misconception: Racism is a Hate not a self-love

Some have labeled Bete-Amhara movement as a racist movement – even if the movement made is clear that their purpose is survival. Any person would tell you that racism is hate towards other groups. It is belief which boasts my group is superior over other races/groups. In my understanding so far – this is not what is happening in Bete-Amhara movement. Coming up with a new idea to empower Amhara people economically should not be criticized for racism. Anyone who do not agree with the idea should come up with a better idea – but know that the status quo is the worst that can happen to Amhara people.

Finally – it is time for a change – especially to Amhara people

For those of us who were born and raised in the region – the pain and the suffering is more than clear. For those of you who live in other regions facing a threat everyday – the pain is even worse. For those who were born and raised in Addis Ababa – I respectfully say – learn what is going on in these areas, then speak it. But – without a doubt – it is time for a change. It shouldn’t necessarily be secession, but any change that walks Amhara a single step to economic equality. More than anything – it is time to discuss the different scenarios in which a positive change can happen to the disadvantaged ምስኪን ወገኔ.

መልካም ነገር ይግጠመን!!!

By #Girma #Derib
Read more
October 20, 2015
no image


ወልቃይት ለም ነው፡፡ ብዙዎች እንደሚስማሙበት በመላው አማራ ምድር ዋናው ምርታማ አካባቢ ወልቃይት ጠገዴ እና አካባቢው ነው፡፡ የትግራይ ሪፐብሊክ ሲታሰብ ከላኮመልዛ እና ጎንደር የሚወሰዱ መሬቶችን ተማምኖ ነው፡፡ ከእነዚህ ሁለት አካባቢዎች ውጭ ትግራይ ማለት ድንጋይና ብናኝ ናት፤ ናሳ የሚለቀውን የማርስ ፎቶ የምትመስል፡፡ እኔ ራሴ እስከማውቀው ትግራይን በደን ለመሸፈን ያልተደረገ ጥረት አልነበረም፡፡ የሚተከለው ችግኝ ግን አንዱም አይጸድቅም፡፡ በመጨረሻ ተራራዎችን ከልሎ ማስቀመጥ እና የሚለሙ ከሆነ ዝም ብሎ ማየት የሚል ስልት ቀየሱ፡፡ እስካሁን ተራሮችን ከልለው ምናልባት የሰሀራ በረሀ ነፋስ ዛፍ አምጥቶ ዘርቶ ያበቅልልን ይሆናል ብለው እየጠበቁ ይሆናል… ቅቅቅ ለምለሚቷ ኣደይ ትግራይ፡፡ የድንጋይ ሪፑብሊክ መመስረት ስለማይቻል እንግዲህ ወያኔዎች አለቅጥ ሊያስፋፏት ግድ ነበረባቸው፤ አለባቸው፡፡ እንደሚመስለኝ የመጀመሪያው ዙር ከዚህ በፊት የተወሰዱትን የአማራ መሬቶች ይዞ የትግራይን ሀይል መገንባት እና ሌላ አቅም ሲገኝ በሶስተኛ ዙር ከፊል ጎንደርን፤ እስከ አምባጊዮርጊስ ድረስ፤ በላኮመልዛ በኩል ደግሞ ወልድያ ድረስ መውሰድ የሚል እቅድ ነው፡፡ ሶስተኛው ዙር እስከ ታላቁ አባይ መድረስ ነው፡፡ ያው ግድብ እየገነቡ አይደል ሱዳን ጥግ፡፡ ይህ ሁሉ የሚፈጸመው ግን በሰላም እንዳልሆነ ያውቁታል፡፡ ለዚህም ብዙ እርምጃ መጓዝ ነበረበቻው፡፡ ሁሉም እርምጃቸው ጸረ አማራ ነው፡፡

እርምጃ አንድ
 

ኢትዮጵያን መቆጣጠርና የትግሬ ከበርቴ መደብ መፍጠር፡፡ የገንዘብ አቅማቸውን በመገንባት የፖለቲካ ስልጣናቸውን በዚሁ ገንዘብ በመታገዝ ማራዘም፡፡ የፖለቲካ ስልጣናቸው መራዘሙ በሚያመጣላቸው እድል የገንዘብ አቅማቸውን የበለጠ ማዳበር፡፡ በዚህም መሀል በተቻለው መጠን ሁሉ እያንዳንዱን ትግሬ ማብቃት፡፡ ማብቃት ማለትም በኢኮኖሚና በማናቸውም በሌላው ረገድ ነው፡፡

እርምጃ ሁለት
 

የመላውን ኢትዮጵያ ገንዘብ በመቆጣጠር የትግሬ ከበርቴ መፍጠሩ ትግራይን ከማልማት ጋር በቀጥታ ይያያዛል፡፡ በዚህም ትግራይን የማበልጸግ ሂደት ጠቃሚው አስተሳሰብ የወራሪነት መንፈስ ነው፡፡ ወራሪ ወይም ቅኝ ገዥ ጥሬ እቃ ወደራሱ አገር በማጋዝ ወደፋብሪካ ምርትነት ለውጦ መልሶ በውድ መሸጥ ነው፡፡ በዚህም ስሌት ትግራይ ውስጥ ፋብሪካዎችን በማስፋፋት ለትግሬ የስራ እድል መስጠት እና ከሌላው ኢትዮጵያ ጥሬ ሀብትን በነጻም ሆነ በርካሽ በማጋዝ ፈብርኮ መልሶ በውድ መሸጥ ነው፡፡ እየተደረገ ያለውም ይሄው ነው፡፡

እርምጃ ሶስት
 

አማራውን ማደህየት፡፡ በንግድም፤ በትምህርትም፤ በሌላ ዘርፍ የአማራን ህዝብ ማፈን እና በተለያዩ ዘዴዎች ማደህየት፡፡ አማራን ማደህየት ለትግሬ መንግስት ፊታውራሪዎች ምን ምን በጎ እድል እንደሚፈጠርላቸው እና እንደፈጠረላቸው መመርመር ነው እንግዲህ፡፡

እርምጃ አራት
 

አማራውን ጸረ አማራ ፕሮፓጋንዳ በመንዛት በታሪክ ጥፋተኛ እንደነበረ እና ጥፋተኝነት እንዲሰማው እና አማራነቱን እንዲሸሸው ማድረግ፡፡ ይህም የሚደረግበትን የዘር ማጥፋ ወንጀል አማራ ነኝ ብሎ በጋራ እንዳይከላከል ያደርገዋል፤ አድርጎታልም፡፡ በረቀቀ ዘዴ ትግሬ እና ሌሎች ብሄሮች ከየራሳቸው ብሄር ጋር ፍቅር ውስጥ ሲወድቁ አማራው ግን አማራነቱን እንዲሸሽ እና ተበታትኖ እዲቀር ሆኗል፡፡ አማራው እንደአማራ ቢመክት ያሰቡትን መስራት እንደማይችሉ የተረዱት ወያኔዎች ይህንን የአማራነት ስሜት ማጥፋት እና በአማራነት መሰብሰብ እና ስለአማራነት መናገር እንደጥፋትና ነውር ነገር እንዲቆጠር ማድረግ ዋና ስራቸው ሆነ፡፡ የዚህ ስውር አላማቸው ደጋፊም አላጡም፡፡ በተለምዶ ራሳቸውን የአንድነት ሀይል ብለው የሚቆጥሩ፤ ከፊሎች በስህተት፤ ሌሎች ደግሞ በመሰሪነት ይህንን የወያኔ ጸረ አማራ ስሜት ቅስቀሳ ሲያካሂዱ ቆይተዋል፡፡ ከእነዚሁም አንዱ አማራ በብህሩ ከተደራጀ ኢትዮጵያ አለቀላት የሚለው ጎደሎ አስተሳሰብ ነው፡፡ እነዚህ መናኛ ፖለቲከኞች እና ስሁታን ምሁራን የአማራ አንድ ላይ መሆን በምን ሂሳብ ኢትዮጵያን ከማፍረስ ጋር እንደተገናኘ ሊያስረዱ አይችሉም፡፡ “አማራ መደራጀት የለበትም፤ ከተደራጀ አገር ይበትናል” የሚለው ስንኩል አስተሳሰብ አማራ ላይ ያደረሰው ተጽእኖ ወያኔ በግልጽ ከሚያካሂደው ጸረ አማራ ቅስቀሳ ጋር ቢተካከል እንጅ አያንስም፡፡ የእነዚህን መናኛ ፖለቲከኞች እና ስሁታን ምሁራን ጸረ አማራ ቅስቀሳም ወያኔ በራሱ መንገድ አማራውን ለመበታተን እና እንዳይሰባሰብ ለማድረግ ይጠቀምበታል፡፡ “አማራ መጣባችሁ እንደድሮው ሊጨቁናችሁ ነው፤ የድሮውን ስርአት ሊመልስ ነው” እያለ እየዞረ የሚቀሰቅሰው ቅስቀሳ የዚሁ ጎደሎ ሀሳብ ተቀጥላ ወይም ደሚራ ውጤት ነው፡፡ መናኛ ፖለቲከኞች እና ስሁታን ምሁራን የሚያስተጋቡት ይህ “አማራ ከተደራጀ አገር ያፈርሳል” የሚል ቅስቀሳ ለወያኔ ጉልበት ፈጥሮለታል፤ አማራ ላይ ለሚያደርገው የሀሰት ክስም ምክንያት ሆኖለታል፡፡ በታሪክ የምናውቀው ግን የዚህን ተቃራኒ ነው፡፡ አማራ ተሰባስቦ ሀይል ባገኘባቸው ጊዜያት ሁሉ አይደለም ኢትዮጵያዊ አለም አቀፋዊ አንጸባራቂ ድሎችን ነው ያስመዘገበው፡፡ ይሁንና በዚህ ጎደሎ አስተሳሰብ የተነሳ አማራ በዛ በኩል በወያኔ፤ በዚህ በኩል በአንድነት አቀንቃኝ ተብየዎች እግር ተወርች ታስሮ ቆየ፡፡ አእምሮ ያለው ሁሉ አማራው በአማራነቱ አለመሰባሰቡ የወያኔን እድሜ እዳራዘመው እና ያልጠበቀውን ጉልበት እንዳጎናጸፈው ይረዳል፡፡

እርምጃ አምስት፡- አማራን መሸበብ
 

አማራን መሸበብ አማራን የማጥፋት እና የትግሬን መንግስት እውን የማድረግ ሂደት ዋናው ዘዴ ነው፡፡ የአማራ መሸበቢያ ሆነው ያገለገሉትም ወልቃይት ጠገዴ እና የድሮው ራስ ገዝ ወሎ ምስራቃዊ እና ሰሜናዊ ክፍሎች ናቸው፡፡ እንደሚታወቀው ትግራይ አለማቀፍ ድንበር የላትም፡፡ ምናልባት አሁን በትግሬና ኤርትራ መካከል ያለው ያልተከለለ ድንበር ካልተቆጠረ በቀር፡፡ ትግራይ በምስራቅ በኩል ከቀይ ባህር ወደ ውስጥ ገባ ብላ በመገኘቷ የባህር በር ችግር አለባት፡፡ ይህንንም ለመፍታት አሰብን በሻእብያ እጅ በይደር በአደራ መልክ አስቀምጠውት እንደነበር ይጠረጠራል፡፡ ምክንያቱም ሸዋን ወይም መሀል አገርን ከቀይ ባህር መነጠል እና መልሶ እዳያንሰራራ ማድረግ የሚለው ቀዳሚ የወያኔ አጀንዳ ስለነበር ከአሰብ ሆነ ብለው ነጥለውታል፡፡ ስለሆነም ከወሎ ቆርሶ አፋር ብሎ ሌላ ክልል መፍጠርና ያንን ክልል በሂደት የትግራይ ክፍል አድርጎ የባህር በር ማግኘት አንዱ ድብቅ አጀንዳ ነው፡፡ ምናልባት ከኤርትራ ጋር አሁን ስለተጣሉ የአሰብን ጉዳይ አስቸጋሪ ያደርገዋል የሚሉ ይኖራሉ፡፡ ነገሩ ትክክል ሊመስል ይችላል፡፡ ይሁንና አንዱ ወዳጃችን እዳለው “የሻዕብያን እና የወያኔን ሴራ እንኳን ሰው ሰይጣን አይደርስበትም”፡፡ ዞሮ ዞሮ ትግራይን ከላይ በተጠቀሰው መንገድ ሀያል መንግስት ማድረግ ማለት ከኤርትራ ጋር የሚኖራቸውን የጥቅም ድርድር አቅም ያሰፋዋል ማለት ነው፡፡ በዚህም ስሌት በቀላሉ የባህር በር ማግኘት ይችላሉ፡፡ ወይም ታላቋን ትግራይ ከፈጠሩ በኋላ ከኤርትራ ጋር በመቀላቀል የጥንቱን የትግራይ ትግርኝ ሪፐብሊክ ህልም ያሳኩ ይሆናል፡፡ ማን ያውቃል? አለም እንደሆነ ተለዋዋጭ ናት!

ወደሁለተኛው እና ዋናው የአማራ መሸበቢያ ወልቃይት ስንመጣ ለትግራይ መንግስት ወልቃይት ጠገዴን፤ ሁመራን፤ ዳንሻን፤ እና ወዘተ መቆጣጠር ብዙ እድል ይፈጥርለታል፤ ፈጥሮለታል፡፡ ከሱዳን ጋር በመገናኘት አለም አቀፍ ድንበር ማግኘት አስችሎታል፡፡ ይህ አሁን በግድ ወደትግራይ የተቀላቀለው ምድር አማራ በጎንደር በኩል ሱዳንን ወደምእራብ በመታከክ ከኤርትራ ጋር የሚገናኝበት ነው፡፡ ይህንን በመቁረጥም ምናልባትም አማራ ከኤርትራ ጋር የሚኖረውን ግንኙነት ማቋረጥ ያስችላቸዋል፡፡ ወልቃይትን መቆጣጠር በሌላ ጎኑ የአማራን ዘር የማጥፋቱ አንዱ አካል ነው፤ የቻለውን ያህልም አጥፍቷል፡፡ በተጨማሪም መሬቱ ለም በመሆኑ የኢኮኖከሚ ጡንቻውን ያዳብርለታል፤ አዳብሮለታል፡፡ በተዘዋዋሪም የአማራን ኢኮኖሚያዊ አቅም ያዳክማል፤ አዳክሟል፡፡ አማራ በወልቃይት በኩል ከኤርትራም ሆነ ከሱዳን ጋር የሚኖረውን ግንኙነት በማቋረጥ፤ ቀስ በቀስም መተማን እስከ ቤኒሻንጉል ድረስ በመውሰድ የአግዳሚ ወንበር ቅርጽ ያላትን ትግራይ መፍጠር አማራን አኮስምኖ፤ አዳክሞ ያስቀረዋል፡፡ በመጨረሻ ለሚደረገው የዘር ማጥፋት ሂደትም ያመቻቸዋል፡፡ ምክንያቱም አማራው መሀል ላይ ታፍኖ በየትም መላወሻ እንዳያገኝ ስለሚደረግ አቅም አልባ ሆኖ ከመጥፋት በቀር ሌላው እድሉ የመነመነ እንዲሆን ያደርገዋል፡፡ ከዚህም ሽበባ በተጨማሪ ከማንኛውም ብሄር ጋር እንዳይተባበር እና መውጫ ቀዳዳ እንዳያገኝ ከሌሎች ብሔሮች ጋር ቁርሾ ውስጥ እንዲገባ ተደርጓል፡፡ አማራ ላይ ለሚደረገው የመጨረሻ ጥፋት ይረዳ ዘንድም በየቦታው እየዞሩ የጥላቻ፤ የበቀልና ቂም ሀውልት ይተክላሉ፡፡ እንግዲህ ማንኛውም አማራዊ ሀይል ወያኔን ለመፋለም ከመነሳቱ በፊት ይህንን ሽበባ ወይም ከበባ እንዴት መስበር እንደሚችል በጥልቀት ማሰብ አለበት፡፡ ቤተ አማራ የዚህን መፍትሄ ይዞአል፤ ተግባራዊ ለማድረግም የመላውን አማራ ንቁ ተሳትፎ እና እገዛ ይጠይቃል፡፡

እናም አማራ ሁሉ ወልቃይት ላይ የሚደረገው የአንተን ጉርቦ ለማነቅ እንጅ ወልቃይትን ብቻ ወስዶ የማይቀር መሆኑን አውቀህ ለራስህ ስትል ከራስህ ጎን ከወልቃይት አማራ ጎን ተሰለፍ፡፡

አገራችን አማራ ወንዛችን ተከዜ፤
ማን ያስገድደናል እምቢ ያልን ጊዜ፡፡
Read more